07/06/2025
የካሊጉላ ክሊፓች እዚህ ፌስቡክ ላይ እያደኑኝ ተቸገርኩ፣ ዛሬም ሁለት ክሊፓች ገጠሙኝ፣ አሁን ስለአንዱ እናውራ፣ ለሁለተኛው እመለሳለሁ፣
"ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት ብቻ ከExport የምታገኝው ገቢ ከ1983 እስከ 1998 (15 ዓመት ጠቅላላ ድምር) በላይ ነው፣ የአስራ-ምስት አመቱ ድምር 7.5 ቢሊየን USD ሲሆን በዚህ ዓመት ብቻ ከ8 ቢሊየን USD በላይ እናገኛለን ብለን እንጠብቃለን፣ በአንድ አመት 8 ቢሊየን ዶላር ማግኝት የምትችል ሀገር 15 ዓመት ሙሉ ምን ትሰራ ነበር ብሎ መጠየቅ ይፈልጋል፣ አዕምሮ ያስፈልጋል" ይላል ካሊጉላ አዕምሮውን በዕጣቱ እየጠነቆለ፣
በዚህ ንግግር ውስጥ አንድ ትልቅ ድንቁርና [እና] አንድ ትልቅ ወንብድና አለ፣ ከድንቁርናው እንጀምር፣
የዚህ ዓመት የውጭ ንግድ ገቢን የዛሬ 20 እና 30 ዓመት ከነበረው ገቢ ጋር ማወዳደር ትልቅ ድንቁርና ነው፣ መወዳደር ካለባቸውም በ Volume እንጂ በዶላር አይደለም፣ ለምሳሌ የዛሬ 25 ዓመት የአለም አቀፍ የቡና ገበያ ዋጋ $0.62/ pound ነበር፣ ዛሬ $4.40/ pound ነው፣ 610% ብልጫ አለው፣ የዛሬ 25 ዓመት የአለም አቀፍ የወርቅ ገበያ ዋጋ $290.25/ ounce ነው፣ ዛሬ $3,331/ ounce ነው፣ 1150% ብልጫ አለው፣ ቀለል ባለ አገላለፅ የዛሬ 25 ዓመት አንድ ኪሎ ወርቅ ተሽጦ የሚገኝው ገንዘብና ዛሬ 100 ግራም ወርቅ ተሽጦ የሚገኝው USD እኩል ነው፣ መልካም የገበያ ሁኔታ (favorable market conditions) የአንድ መንግስት ስኬት ተደርጎ የሚቆጠረው ካሊጉላ ጭንቅላት ውስጥ ብቻ ነው፣ [በነገራችን ላይ በ Volume መወዳደሩ ራሱ አግባብ ነው እያልኩ አይደለም፣ አንድ በህይወት ያለች ሀገር በትንሽ በትንሹም ቢሆን የውጭ ንግድ መጠኗን መጨመሯ ተፈጥሯዊ ነው፣] ...ወደ ውንብድና እንለፍ
ካሊጉላ ከ1983 እስከ 1998 ያለውን ዳታ የፈለገው ለውንብድና እንዲመቸው ነው፣ ለማጭበርበር ነው፣ በተጠቀሱት 15 ዓመታት ከውጭ ንግድ የተገኝ ተብሎ የሚጠቀሰው ከቡና፣ ከቅባት እህል፣ አበባ፣ ጨርቃጨርቅ ወዘተ ሽያጭ የሚገኝውን የውጭ ምንዛሬ ነበር፣ ዛሬ የኢትዮጵያ እየር መንገድ የሚስገኝው የውጭ ምንዛሬ እንደ export ተቆጥሮ ሪፖርት እየተደረገ ነው፣
በ2023 ከውጭ ንግድ የተገኝ ገቢ ተብሎ ሪፓርት የተደረገው 10.8 ቢሊየን USD ነው፣ ከዚህ ቁጥር ውስጥ እንደ ቡና፣ ሻይ፣ የቅባት እህል፣ ቆዳ፣ ወርቅ ወዘተ ተልኮ (Merchandise-Goods Exports) የተገኝው ግን 2.8 ቢሊየን USD ብቻ ነው፣ 7.4 ቢሊየን ብሩ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ያስገኝው የውጭ ምንዛሬ ነው፣ የተባበሩት መንግስታት COMTRADE database ውስጥ ገብቶ ሊያረጋግጠው ይችላል፣
የዛሬ 10 ዓመት (i.e 2015 ዓ.ም) ከምርት ንግድ (Merchandise-Goods Exports) የተገኝው 2.91 ቢሊየን USD ነው፣ የዛሬ ሁለት ዓመት ከተገኝው የውጭ ምንዛሬ 100 ሚሊየን USD ብላጭ አለው፣ የአለም ገበያ ዋጋ ልዩነቱን ታሳቢ ካደረግን የዛሬ 10 ዓመት ከውጭ ንግድ የተገኝው ገቢ በካሊጉላ አምስት ዓመታት ከተገኝው በላይ ነው፣ አዕምሮ ያስፈልጋል ነው ያለው?
*** ይህ ሁሉ መፀሐፍ ባለበት ቦታ ድንቁርና እንደ ጎርፍ ሲወርድ ገጥሞኝ አያውቅም፣
#ካሳ