Abyssinia

Abyssinia Positive thinking, or optimistic attitude, is the practice of focusing on the good in any situation.
(3)

ዘአኢኮኖሚስት በዘገባው አብይ አህመድን እንዲህ ሲል ለዘገባው ርእስ ሰጥቶታል “ረሀብን የሀይል መጠቀሚያ ያደረገ” ሲል የአብይ አህመድን ሀገሪቱን አይቀሬ ክፍፍል እና መፍረስ ሊዳርጋት እንደሚ...
05/31/2026

ዘአኢኮኖሚስት በዘገባው አብይ አህመድን እንዲህ ሲል ለዘገባው ርእስ ሰጥቶታል “ረሀብን የሀይል መጠቀሚያ ያደረገ” ሲል የአብይ አህመድን ሀገሪቱን አይቀሬ ክፍፍል እና መፍረስ ሊዳርጋት እንደሚችል ሀተታውን አስቀምጧል።

በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ኃላፊው በታጣቂዎች ተገደሉበሰሜን ወሎ ዞን የአንጎት ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ተመስገን ያረጋል በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይ...
05/31/2026

በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ኃላፊው በታጣቂዎች ተገደሉ

በሰሜን ወሎ ዞን የአንጎት ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ተመስገን ያረጋል በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ።

ወረዳው ባወጣው አጭር መግለጫ አቶ ተመስገን "የተሰጣቸውን የህዝብ አደራ ለመወጣት በስራ ተጠምደው ለእረፍት ትናንት ማታ ወደ ቤታቸው ሊገቡ ሲሉ በሰርጎ ገብ ታጣቂዎች ጥይት ተመተው ገና በ40 ዓመታቸው ህይወታቸው ማለፉን" አሳውቋል።

"አቶ ተመስገን እንደ አንድ የህዝብ አደራ እንደተቀበለ አመራር ወረዳውን በልማት መስክ ለማሰጠቀም፣ የወረዳው ማህበረሰብ ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ በከፍተኛ ቁጭት እየሰሩ የሚገኙ አመራር" እንደነበሩ በመግለጫው ላይ ሰፍሯል።

መግለጫው የገዳዮቹን ማንነት "ሰርጎገብ" ከማለት ውጭ በግልፅ አልጠቀሰም።

የአመራሩ ስርዓተ ቀብር በአንጎት ወረዳ አሁን ተገኝ ከተማ በሚገኘው ተከስቴ ቅድስት ስላሴ ቤተ-ክርስቲያን በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6 ስዓት ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት መፈፀሙ ተሰምቷል።

05/31/2026
ፒአኤስጂ ዋንጫ በላ
05/31/2026

ፒአኤስጂ ዋንጫ በላ

''ዓመታት ያስቆጠረን ተግባራዊ ልምድ በወረቀት መለካት አይቻልም!  ለሙያችን ክብር፣ ለኑሯችን ዋስትና የሾፌሮች ድምፅ ይሰማ!''አሽከርካሪነት መሪ ማዞር ብቻ አይደለም፤ ሌሊት ከቀን፣ በፀሐይ...
05/30/2026

''ዓመታት ያስቆጠረን ተግባራዊ ልምድ በወረቀት መለካት አይቻልም! ለሙያችን ክብር፣ ለኑሯችን ዋስትና የሾፌሮች ድምፅ ይሰማ!''

አሽከርካሪነት መሪ ማዞር ብቻ አይደለም፤ ሌሊት ከቀን፣ በፀሐይና በብርድ፣ ሕይወትንና ንብረትን ከቦታ ቦታ የሚያሻግር የአገር የጀርባ አጥንት የሆነ ከባድ ሙያ እንጂ፤ ዛሬ ግን ይህ የዕለት ተዕለት ድካማችንና ለአገር የምናበረክተው አስተዋጽኦ ተረስቶ፣ በነባር አሽከርካሪዎች ላይ የተጫነው አዲሱ ''የብቃት ምዘና ፈተና"በብዙዎቻችን ሕይወትና የሥራ ዋስትና ላይ ትልቅ ስጋት ደቅኗል።

ይህንን አሠራር በጥብቅ የምንቃወምባቸውና ድምፃችን እንዲሰማ የምንጠይቅባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች፡-

1. ዓመታት ያስቆጠረን ተግባራዊ ልምድ በወረቀት መለካት አይቻልም! አንድ አሽከርካሪ ብቁ የሚሆነው ለዓመታት በአስቸጋሪ መንገዶች ላይ ካሳለፈው የተግባር ልምድ፣ ከገጠመው ፈተናና ካዳበረው ጥንቃቄ እንጂ በፈተና አዳራሽ በሚሰጥ ጥያቄና መልስ አይደለም።

ዛሬ "ብቃት የላችሁም" ተብለው ከሥራ ሊገለሉ የተዘጋጁት ሾፌሮች፣ ለአሥርተ ዓመታት አገር ያሻገሩና በመንገድ ላይ የሸበቱ ባለሙያዎች ናቸው በተግባር የታየን ዕውቀት በንድፈ-ሐሳብ (Theory) መመዘን ፍትሃዊ አይደለም።

2. የአሠራር ግልጽነት መጓደልና የተጓደሉ መሠረተ-ልማቶች ምዘናው ከመጀመሩ በፊት ለአሽከርካሪው በቂ ግንዛቤ፣ ሥልጠናና ራሱን የሚያዘጋጅበት ጊዜ አልተሰጠም።

በቂ ዝግጅት ሳይደረግ፣ የመፈተኛ ሥርዓቶቹና ግብዓቶቹ ባልተሟሉበት ሁኔታ አሽከርካሪውን በቀጥታ ወደ ፈተና ማስገባት የብዙዎችን ዕድል ማጨለም ነው። ይህ አሠራር ሙያን ከማሻሻል ይልቅ፣ ሾፌሩን ለከፍተኛ ውጥረትና እንግልት እየዳረገ ይገኛል።

3. የብዙ ሺህ አሽከርካሪዎች የኑሮ ዋስትና አደጋ ላይ መውደቅ ከእያንዳንዱ አሽከርካሪ ጀርባ የሚተዳደር ቤተሰብ፣ የሚያድጉ ልጆችና የሚከፈል የቤት ኪራይ አለ።

በአገራችን አሁን ባለው ተጨባጭ የኑሮ ውድነት ላይ፣ ይህ ምዘና በሺዎች የሚቆጠሩ ሾፌሮችን ያለምንም አማራጭ ከሥራ ውጭ ሊያደርግ ይችላል። ይህ ደግሞ በቤተሰቦች ላይ ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ የትራንስፖርትና የሎጂስቲክስ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ቀውስ መፍጠሩ የማይቀር ነው።

4. ከቅጣትና ከማግለል ይልቅ ማበረታታት ይቀድማል፣ የመንገድ ደኅንነትን ማስጠበቅ የሚቻለው አሽከርካሪውን በማሳደድ፣ ፍቃድ በመከልከል ወይም ፈተና በማብዛት አይደለም።

ይልቁንም ነባር አሽከርካሪዎች ያሉባቸውን ክፍተቶች ለይቶ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን በነጻ በመስጠት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማቶችን በማሻሻልና ለአሽከርካሪው ተገቢውን ክብርና ማበረታቻ በመስጠት መሆን አለበት።

''መልእክታችን ለመንግሥትና ለሚመለከታቸው አካላት ይደርስ ዘንድ እንጠይቃለን!''

እኛ ሕግ አክባሪና ለአገራችን የምንለፋ ሠራተኞች ነን። የመንገድ ደኅንነት እንዲጠበቅ ከማንም በላይ እንፈልጋለን። ነገር ግን የነባር አሽከርካሪዎችን ልምድና ሕይወት ከግምት ውስጥ ያላስገቡ፣ አግላይና አስገዳጅ የሆኑ የምዘና ሥርዓቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ወይም እንዲሻሻሉ እንጠይቃለን!

የአሽከርካሪዎች መብትና የሥራ ዋስትና ይከበር!

የሾፌሮች እሮሮ

''ቱሉ ሚልኪ የደም ምድር'' 1ቀን ተቆጠረ ማንም ምንም ያለ አካል የለም!ሀዘኑን የሚያብሰው የታጋቾችን ሞት፣ ስቃይና እንግልት ክደው ምንም እንዳልተፈጠረ ሆነው ስናይ ነው። ግንቦት 20/09...
05/29/2026

''ቱሉ ሚልኪ የደም ምድር'' 1ቀን ተቆጠረ ማንም ምንም ያለ አካል የለም!

ሀዘኑን የሚያብሰው የታጋቾችን ሞት፣ ስቃይና እንግልት ክደው ምንም እንዳልተፈጠረ ሆነው ስናይ ነው።

ግንቦት 20/09/2018 ኦሮሚያ ክልል ቱሉ ሚልኪ እና ጎሀፂዮን መሀከል 2አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪ ታፍኖ ተወስዶ፣12 ተሳፋሪ ደግሞ በታጠቁ አጋቾች ተገድለው ሚዲያው ግን ስለ ጃኒ አዶናይ መለያየት ያወራል።

የሚገርመው በደልን ቆሞ ያየው ያላወገዘው ሁሉ ''ነገ ያ በደል በቤቱ እንደሚገባ አለማወቁ ነው። ''ዛሬ የንጹሃንን ጉዳት እያፌዝክ በሞታቸው አያላገጥክ ያለፍክ ሁሉ ይችን ፅዋ ትጎነጫታለህ።''

Abyssinia

"ከቻላችሁ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ሁኑ!" ሁለት አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪ በታጣቂዎች ታግቶ የተረፈ የለም''ለምርጫ መቀስቀሻ ሲሆን ሚዲያው ክፍት ነው ለዜጎች ሞት ዜና መስራት ሀጢያት ነው በተ...
05/29/2026

"ከቻላችሁ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ሁኑ!" ሁለት አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪ በታጣቂዎች ታግቶ የተረፈ የለም''

ለምርጫ መቀስቀሻ ሲሆን ሚዲያው ክፍት ነው ለዜጎች ሞት ዜና መስራት ሀጢያት ነው በተለይ ሞት ከወደ አማራ ክልል ከሆነ ግድ አይሰጣቸውም። በውጭ ሀገራት ጀኔራል ሞተ ንፁሀን ተጎዳ እያሉ ሲያደነቁሩን የሚውሉት የመንግስት ሚድያዎች ትንፍሽ አላሉም።

ይባስ ብለው የአማራን ህዝብ መታገት፣ መጎሳቆል፣ መራብ መጠማት፣ መገደል እንደ መበልፀግ ተቆጥሮ ከራሱ ማህፀን የወጡ መሪህን ነን የሚሉት ''የአማራ ሕዝብ እንደ ብልፅግና የተመቸው እና የተሻለ ዘመን መቸም አያገኝም አግኝቶም አያውቅም ይባልልናል።''

በሰሞኑ በባሕርዳር ተገኝተው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ያደረጉት ንግግር፤ የብርጋዴር ጀኔራል አሳምነው ፅጌን ቃል እንድናስታውስ ያስገድዳል........

"ከቻላችሁ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ሁኑ!" ህዝቡ ራሱን ማደራጀት አለበት ብዬ አምናለሁ፡፡ ከዚያ በላይ ራሱን ማዘጋጀት አለበት ብዬ አስባለሁ፡፡

Because'' አማራን ለማፍረስ ያልተሰራ ስራ የለም፡፡ ይኼ ደግሞ ምድር ላይ የተቀበረ ሳይሆን ከምድር ወጥቶ እያየነው ነው፡፡

So ይኼ ትውልድ ይህን ታሪካዊ ጊዜ ካልተሻገረ ታሪካዊ ስህተት ይፈጽማል፡፡ ብ/ጄኔራል አሳምነው ፅጌ

አባቶቻችን አንዳንድ ጊዜ የሽምግልና የድርድር ንግግር አታድርጉ። ''just ህሊናችሁና መሬት ላይ ያለውን እውነታ ለመናገር ሞክሩ፡፡'' ከቻላችሁ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ሁኑ!!" ይላል!

ተመልክቱ በየሳምንቱ እና በየቀኑ በሚባል ደረጃ ''በጎሀፅዮን እና አሊዶሮ ላይ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚገቡ እና የሚወጡ ንፁሀን ዜጎች ከለውጡ መንግስት (ከ7እና8 አመታት በፊት ጀምሮ) በአማራነታቸው ብቻ ተመርጠው በተመሳሳይ ቦታ እየታገቱ ይገደላሉ።

አሁን አሁንማ ይባስ ተብሎ የነዚህ መንገደኞች መታገት እና መሞት ዜና መሆኑም ቀርቶ፣ እንደ ተራ ወሬ ታይቶ እየታለፈ መሆኑ እጅግ ያሳዝናል።

ሰላም ለኢትዮጲያ!
ሰላም ለህዝባችን!
ጦርነት ይብቃ!

05/29/2026

በዘር የምንባለው አንሶን በሀይማኖት እንድንባላ የሀይማኖት ጥላቻ እንዲኖረን ከሚያደርጉ ግብረ-ገብነት ከጎደላቸው ተጠንቀቁ። እስኪ የዚህን ኡዝታዝ ትምህርት ስሙና አስተያየት ስጡበት?

''ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣናቸው ተባረሩ''የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ እና የቅርብ ሰው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን መነሳታቸውን መሰረት ሚዲያ ዘግቧል። ዲያቆን ዳንኤል የፋና ብሮድ...
05/28/2026

''ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣናቸው ተባረሩ''

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ እና የቅርብ ሰው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን መነሳታቸውን መሰረት ሚዲያ ዘግቧል።

ዲያቆን ዳንኤል የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩ ሲሆን፤ ከተቋሙ ሰራተኞች በተነሳባቸው ቅሬታ ምክንያት ከቦርድ ሰብሳቢነታቸው ተነስተዋል ተብሏል።

በምትካቸውም የኮሙኒኬሽን ሚኒስትሯ ወይዘሯ እናትአለም መለስ ተተክተዋል። ይህን የስልጣን ሽግሽግ በተመለከተ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንም ሆነ ከመንግሥት በኩል የተባለ ነገር የለም።

Abyssinia

ቋርፍ ምግብ ከምን ይሰራል...⁉️የዋልድባ ገዳም አባቶች "የሰው ሰገራ" ይመገባሉ የሚል ወሬ በሰፊው ማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተናፈሰ ነው። ምክኒያቱ ደግሞ እሸቱ መለሰ ከ ቀናቱች በፊት ወደ ...
05/27/2026

ቋርፍ ምግብ ከምን ይሰራል...⁉️

የዋልድባ ገዳም አባቶች "የሰው ሰገራ" ይመገባሉ የሚል ወሬ በሰፊው ማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተናፈሰ ነው። ምክኒያቱ ደግሞ እሸቱ መለሰ ከ ቀናቱች በፊት ወደ ገዳሙ ገብቶ ይህ በምስሉ ላይ ያለውን ምግብ ሲመገብ ስለታየ ነው።

እውነታው ግን ከዚ የራቀ ነው...

ይህ ምግብ ቋርፍ ይባላል... ቋርፍ በተለይ በሃይማኖታዊ ሥርዓትና በብሕትውና ሕይወት ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለው፣ በዋልድባ ገዳም የሚገኙ መናኞች መነኮሳት የሚመገቡት እጅግ ታዋቂ የዛፍ ወይም የዕፅዋት ሥር ነው።

በገዳማዊው አካባቢ በዱር ውስጥ የሚበቅል፣ እንደ ድንች ወይም እንደ ካሮት ከመሬት በታች የሚገኝ የምግብ ሥራሥር ነው። እጅግ መራራ ሲሆን የራሱ የሆነ መንፈሳዊ ትርጉም አለው...!

ልክ እንደ ድንች ወይም እንደ ሽንኩርት ላይኛው ቆዳው ተልጦና ተቀርፎ ነው ለምግብነት የሚዘጋጀው ከዚህም የተነሳ "ቋርፍ" የሚለው ስም "መቅረፍ/መለጥ" ከሚለው ቃል የመጣ ነው።

በገዳሙ ያሉ አባቶች ዓለማዊ ምግብን ትተው፣ ሥጋቸውን ለማድከም እና ለጸሎት እንዲመች አድርገው የሚመገቡት ዋነኛ የቁራሽ ምግብ ነው።

አንዳንድ አክራሪ ሃይማኖተኞች ለብሽሽቅና አብሮ የመኖር ባህላችንን ለመናድ የፈጠሩት አሉባልታ ነው።

Address

Virginia Beach, VA

Telephone

+251934647389

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abyssinia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Abyssinia:

Share