Abyssinia

Abyssinia Positive thinking, or optimistic attitude, is the practice of focusing on the good in any situation.
(2)

ሰበር‼️ ድጋፉን ቃል ስለገባሁ በሌላ በኩል ለተረጅዎች ይደርሳል'' አቶ ወርቁ አይተነው አስቸኳይ ምላሽ ሰጡበትላንትናው ምሽት በሚደረግ በደብረብረሃን መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖቻችን በቲክቶ...
12/25/2025

ሰበር‼️ ድጋፉን ቃል ስለገባሁ በሌላ በኩል ለተረጅዎች ይደርሳል'' አቶ ወርቁ አይተነው አስቸኳይ ምላሽ ሰጡ

በትላንትናው ምሽት በሚደረግ በደብረብረሃን መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖቻችን በቲክቶክ በሚደረግ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ 15ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል የገባሁ ሲሆን ድጋፉን በአግማስ ኢትዮጵያ (Agmas Ethiopia Charity organization) ለመስጠት ወስኘ ነበር።

ነገር ግን በአግማስ ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅት
በኩል የወጣ መግለጫ ተመለከትኩ ለፖለቲካ እንጂ ለርዳታ አይደለም የለገሰው አንቀበልም በማለታቸው እያዘንኩ ቃል የገባሁትን 15ሚሊዮን ብር ለታቀደው እና ቃል ለገባሁት አላማ በደብረብረሃን መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖቸ ድጋፉን በሌላ በኩል የማደርስ መሆኑን አሳውቃለሁ።

ማጠቃለያ:-
አግማስ ኢትዮጵያ የኔን ድጋፍ ለፓለቲካ አላማ ነው በኛ በኩል የመጣው ብለው አስበው ከሆነ በትልቁ ተሳስተዋል። ለፖለቲካ ማዋል ብፈልግ ሽህ መንገዶች አሉ እኔ ግን ይህን በሴራ ፖለቲካ ከቄሄው እና ከእርስቱ ተፈናቅሎ ፍዳውን የሚበላ መከረኛ የአማራ ህዝብ ለፖለቲካ ጥቅም የማውል ተራ ሰው አይደለሁ።

በማለት አቶ ወርቁ አይተነው መልዕክት አስተላልፈዋል!

  '' ከ60ሚሊዮን ቅፈላ እስከ 15ሚሊዮን ክልከላ'' ከሀይማኖት ገልተኛ ነኝ ያለው ሀይማኖተኛ ተቋም አግማስ ኢትዮጵያ (Agmas Ethiopia Charity organization) ''ይህ መ...
12/25/2025

'' ከ60ሚሊዮን ቅፈላ እስከ 15ሚሊዮን ክልከላ'' ከሀይማኖት ገልተኛ ነኝ ያለው ሀይማኖተኛ ተቋም አግማስ ኢትዮጵያ (Agmas Ethiopia Charity organization) ''ይህ መረጃ ሚዲያችንን አይወክልም''

የአቶ ወርቁ አይተነውን የ15ሚሊዮን ብር ድጋፍ አልቀበልም ያለው አግማስ ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ድርጅት ምን አስቦ ነው? ለፓለቲካስ ቢሆን መጠለያ ጣቢያ የሚገኙት እናቶች ለጉብኝት አይደለም የመጡት ''ወገኖቻችን የተፈናቀሉትም፣ እየተራቡ ያሉትም በፖለቲካ እንደሆነ ይታወቃል ።

አቶ ወርቁ አይተነው ህዝብ እንደሚያውቃቸው በፖለቲካ ሸፍጥ እና በማንነታቸው ተመርጠው ከሀገራቸው የተባረሩ መሆናቸው እየታወቀ ድጋፍ አንቀበልም ፖለቲካ ነው ማለት በራሱ ሌላ ፖለቲካ ነው።

ለነዚያ በደብረብርሃን መጠለያ ጣቢያ ለሚፈሱ የደም እምባዎች ማበሻ በቻሉት መጠን በለገሱ አግማስ ኢትዮጵያ (Agmas Ethiopia የሚባለው የበጎ አድራጎት ድርጅት ባይ ነኝ ያወጣው መግለጫ አሳፋሪ ነው፣ ፖለቲካም ነው።

ስለ ድርጅቱ ብዙ መረጃዎች እየወጡ ነው፣ በውስጥ ከብዙ አሳፋሪ ስራዎቹ በጥቂቱ ደርሰውናል፣ ይህን 15ሚሊዮን ብር አልቀበልም ማለቱ እንደ ምንጮቻችን ዘገባ ከሆነ የሚጎዳው መጠለያ ጣቢያ ከሚገኙት እናቶች ይልቅ በሀይማኖት እና ለፖለቲካ መሸቀጫ የተደራጀው አግማስ ኢትዮጵያ ነው ብለውናል። እናቶችማ ችግሩን ለምደውታል፣

ሌላው አሳፋሪው ተግባር የበጎ አድራጎት ድርጅት ነኝ ባዩ ተቋም በደብረብረሃን መጠለያ ጣቢያ ተገኝቶ በሀይማኖት ከፋፍሎ ሙስሊሞች በዚህ፣ ክርስቲያኖች በዚህ በማለት ቦታ ለይቶ እርዳታ ሰጠሁ ብሎ እንደተመለሰም ከስፍራው መረጃ ደረሶናል። በነዚህ ህፃናት እና እናቶች መሸቀጥ ነው ፖለቲካ ስለዚህ እንድህ አይነቱም በሀይማኖት እና በፖለቲካ ስም ለመጣ ተቋም ጊዜና ገንዘብ ማባከን አይገባም እና ሳይረፍድ ይህን በተለይ በአማራ ህዝብ ላይ በሀይማኖት መከፋፈል እንድፈጠር ተግቶ የሚሰራ ተቋም ማባረር ተገቢ ነው።

ሌላው ስለ አግማስ ኢትዮጵያ የደረሱን አስነዋሪ ተግባር ብዙ ናቸው አግማስ ኢትዮጵያ ማለት በጥቃቅን ሙስሊም ነን ባዮች ግን ህዝበ ሙስሊሙን የማይወክሉ እና ከመንግስት አካላት ጋር ግንኙነት ባላቸው ሙስሊም ተዋቂ ሰዎች ብቻ የተቋቋመ ተቋም ሲሆን በበጎ አድራጎት ስም ሌላ አላማ ያለው ስለመሆኑ የሚጋለጥበት ጊዜ አሁን ነው ተብሏል።

ይህ አሁን በበጎ አድራጎት ስም የመጣው ቡድን ህዝብ እንደሚያውቀው በሳውዲ አረቢያ አንድት ሚስኪን የሞት ፍርድ ተፈረደባት ብለው ከ60ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር በላይ ከሰበሰቡት ህዝበ ሙስሊሙን የማይወክሉ ሙስሊም ቡድኖች የተመሰረተ ስለመሆኑ ታውቋል እነሱ ባወጡት መግለጫ አይነት ሳይሆን ሀይማኖትን እና ዘርን መሰረት አድርጎ የሚቀሰቅስ ተቋም መሆኑ የተረጋገጠ ነው።

የሞት ፍርድ ተፈረደባት ብለው ነጋ ጠባ አስጨኸው ከ60ሚሊዮን ብር በላይ ሰብስበው እንደነበር የሚታወቅ ነው፣ የተሰበሰበውም ገንዘብ ልጅቱ ሳትወጣ ሪል እስቴት እና ቅንጡ መኪና ገዝተውበታል የተባለ ሲሆን ይህ ቡድን ነው እንግድህ ከሀይማኖት እና ፖለቲካ ነፃ ነኝ በሚል ዘፈን ተከስቶ ለህፃናት እና እናቶች የተለገሰ ገንዘብ አንቀበልም ብለው መግለጫ ያወጡት።

ከኢትዮጵያ እስከ ሳውድ አረቢያ የተዘረጋ መረብ ያለው በኢትዮጵያ ሙሉ በሚባል ደረጃ የሙስሊሙ ኡስታዞች፣ሸኮች፣ ቃሪዎች፣ ቲክቶከሮች፣ ዩቱዩበሮች ሳይቀር ተደራጅተው የተሰማሩበትን ተቋም ከሀይማኖት ገልተኛ ነው ማለት ራሱ ፖለቲካ ነው።

ብዙ መረጃዎች እየደረሱን ነው እንደአስፈላጊነቱ ለህዝብ ይፋ የምናደርግ ይሆናል?

12/24/2025
ይሄ ነገር እውነት ነው?
12/24/2025

ይሄ ነገር እውነት ነው?

የቱ ነው መታሰር ያለበት?
12/24/2025

የቱ ነው መታሰር ያለበት?

12/23/2025

ሰዎች በረሀብ አንጀታቸው ተጣብቆና አጥንታቸው ገ'ጦ በሲቃ እየቃተቱ ባሉበት ሰዓት ለተራቡ ወገኖች የደረሱትን ቲክቶከሮች፦"አርፋችሁ ተቀጡ! አያገባችሁም!"እያላችሁ ለማስፈራራት የምትሞክሩ ጨካኞች፤ እናንተ ራሳችሁ አርፋችሁ ተቀመጡ!
ማን እንዲደርስላቸው ነው "አርፋችሁ ተቀመጡ!" የምትሏቸው? ነው ወይስ "ተዋቸው ይሙቱ!'እያላችሁ ነው?

እንደ መንገድ ላይ ስልክ፤ በጎረሳችሁት ሳንቲም ልክ ለምትጮኹት ለእናንተ፤ ስለ ሰብዓዊነት ማስረዳት፤ በጥቁር ድንጋይ ላይ ውሃ እንደማፍሰስ ነው።

ቲክቶከሮች በርቱ! ጠንክሩ!!ለወገኖቻችን በምንችለው አቅም እንደግፋለን።

Via Dereje Habtewold

Address

Virginia Beach, VA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abyssinia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Abyssinia:

Share