12/25/2025
ሰበር‼️ ድጋፉን ቃል ስለገባሁ በሌላ በኩል ለተረጅዎች ይደርሳል'' አቶ ወርቁ አይተነው አስቸኳይ ምላሽ ሰጡ
በትላንትናው ምሽት በሚደረግ በደብረብረሃን መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖቻችን በቲክቶክ በሚደረግ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ 15ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል የገባሁ ሲሆን ድጋፉን በአግማስ ኢትዮጵያ (Agmas Ethiopia Charity organization) ለመስጠት ወስኘ ነበር።
ነገር ግን በአግማስ ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅት
በኩል የወጣ መግለጫ ተመለከትኩ ለፖለቲካ እንጂ ለርዳታ አይደለም የለገሰው አንቀበልም በማለታቸው እያዘንኩ ቃል የገባሁትን 15ሚሊዮን ብር ለታቀደው እና ቃል ለገባሁት አላማ በደብረብረሃን መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖቸ ድጋፉን በሌላ በኩል የማደርስ መሆኑን አሳውቃለሁ።
ማጠቃለያ:-
አግማስ ኢትዮጵያ የኔን ድጋፍ ለፓለቲካ አላማ ነው በኛ በኩል የመጣው ብለው አስበው ከሆነ በትልቁ ተሳስተዋል። ለፖለቲካ ማዋል ብፈልግ ሽህ መንገዶች አሉ እኔ ግን ይህን በሴራ ፖለቲካ ከቄሄው እና ከእርስቱ ተፈናቅሎ ፍዳውን የሚበላ መከረኛ የአማራ ህዝብ ለፖለቲካ ጥቅም የማውል ተራ ሰው አይደለሁ።
በማለት አቶ ወርቁ አይተነው መልዕክት አስተላልፈዋል!