11/14/2025
የህሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ በአደራዳሪዎች የሚመራ የምክክር መድረክ እንዳይካሄድ እያገደ መሆኑን ከሰሱ።
ሊቀመንበሩ አክለውም፣ ህወሓትም ሆኑ ዓለም አቀፍ አደራዳሪዎቹ፣ እንዲህ አይነት የጋራ ውይይት እንዲካሄድ በተደጋጋሚ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
ዶ/ር ደብረጽዮን ይህንን ያሉት ለድርጅቱ ይፋዊ ሚዲያ 'ወይን' (Woyen) በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በፕሪቶሪያ ስምምነት እና በህወሓት ህጋዊ ሁኔታ (legal status of the TPLF) ዙሪያ ለሰጡት አስተያየትም ምላሽ ሰጥተዋል።
"አደራዳሪዎቹም ሆኑ እኛ [ህወሓት] ተገናኝተን በስምምነቱ አፈጻጸም ላይ መወያየት እንፈልጋለን" ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ህወሓት ጥያቄውን በተደጋጋሚ ማቅረቡንና አደራዳሪዎቹም ለውይይት መገፋፋታቸውን አስረድተዋል።
ነገር ግን፣ "በአደራዳሪዎች ፊት በሚደረግ ውይይት ላይ ለመሳተፍ 'እምቢ ያለው የፌደራል መንግስት ነው'" ሲሉ ዶ/ር ደብረጽዮን ወቅሰዋል።
ሊቀመንበሩ በዚሁ ቃለ መጠይቅ ላይ አደራዳሪ አካላትንም ተችተዋል። ስምምነቱ እንዲተገበር ከመወትወት እና ምክር ከመስጠት ባለፈ፣ በፌደራል መንግስት ላይ "በቂ ጫና እያደረጉ አይደለም" (failing to exert adequate pressure) ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
በተለይም የቀድሞው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሃመር [Mike Hammer]፣ ስምምነቱ እንዲተገበር ከፍተኛ ግፊት ያደርጉ እንደነበር አስታውሰው፣ ከሳቸው መውጣት በኋላ (ወይም ምትክ አለመመደቡ) "ግልጽ ክፍተት ታይቷል" ብለዋል።
#ዜና #ሰበር #ሰበርዜና #ሀሳብ