Hasab Today

Hasab Today HasabToday
(1)

06/13/2025

የእስራኤል ጥቃት ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ?

  📈እስራኤል በኢራን ላይ ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከሰነዘረች በኋላ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 13 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ከ2020 በኋላ በቀን ውስጥ በዚህ ደረጃ ሲጨምር ከፍተኛው ነው ተብሏል።አሁ...
06/13/2025

📈

እስራኤል በኢራን ላይ ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከሰነዘረች በኋላ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 13 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

ከ2020 በኋላ በቀን ውስጥ በዚህ ደረጃ ሲጨምር ከፍተኛው ነው ተብሏል።

አሁን ያለው ውጥረት በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ መቆራረጥ እንዳይፈጥር ተሰግቷል።

በጥቃቱ መክንያት በዓለም ገቢያ ፈጣን እርምጃዎች እየተስተዋሉ ነው። የአክሲዮን ገቢያዎች ተዳክመዋል፤ ባለሀብቶች እንደ ወርቅ፣ ስዊስ ፍራንክ እና የጃፓን የን ያሉ ደህንነታቸው የተጠበቀ ወደሆኑ ንብረቶች እየተጣደፉ ነው።

ተንታኞች ውጥረቱ ተባብሶ በዚሁ ከቀጠለ ሁኔታው ​​የዓለምን የኃይል ገበያ የበለጠ ሊያናጋ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

ቀጣዮቹ 72 ሰዓታት ይህ ዋጋ በዚሁ ለመቀጠሉ ወይም ለመባሱ ወሳኝ ሰዓታት ናቸው ተብሏል።

ኢራን በቀን እስከ 3.3 ሚሊዮን በርሜል ታወጣለች፣ ይህም ከዓለም አቀፍ አቅርቦተለ 3 በመቶውን ይሸፍናል።

Source: BBC , CNBC
#ኢራን 🇮🇷

ቅድስት ድንግል ማርያም የልባችሁን መልካም መሻት ትሙላላችሁ !እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዐል አደረሳችሁ"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም። በህግ...
05/09/2025

ቅድስት ድንግል ማርያም የልባችሁን መልካም መሻት ትሙላላችሁ !

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዐል አደረሳችሁ

"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም። በህግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።" ይላል ታላቁ ሊቅ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም፡፡ ግንቦት አንድ ቀን በሊባኖስ ተራራ ላይ የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 86፡1-7 “መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡” በማለት አስቀድሞ ትንቢት ተናግሮላታል፡፡ “የተቀደሱ ተራሮች” ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ትንቢቱንና የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ “እመቤታችን በአባቷ ከንጉሡ ከዳዊት፤ በእናቷም ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው” ብላ ታስተምራለች፡፡ የእመቤታችን የቅድስት ማርያም ልደት ከሰው ሁሉ ልደት ይልቅ የከበረ ለአምላክ ሰው መሆን፣ ለተስፋው ቃል መፈጸም መንገድ የጠረገ ነው፡፡

ከዐበይት ነቢያት የሚቆጠረው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ “ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡” በማለት በ11÷1 ምዕራፍ ይናገራል፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም አበባ የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት የተናገረው ትንቢት “ከዕሴይ ስር ትወጣለች” ያላት አበባን የምታስገኝ በትር፣ አምላክ ሰው የሆነባት፣ ድንቅ የተዋሕዶ ምሥጢር የተፈጸመባት በግንቦት አንድ ቀን የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። እመቤታችን ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷ ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ።

በጊዜው ካህናቱ የመካኖችን መብዓ አይቀበሉም ነበርና፣ ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘን እንዲያርቅላቸው በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽመው ይማልዱ ነበርና የልባቸውን መሻት ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡ በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረዶ የመልአኩን ብስራት ለቅድስት ሐናም ነገራት። እርሷም ቃሉ እውነት እንደሆነ አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች፤ ሴትም ወንድም ብትወልድ በዘመናቸው ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ልታደርግ ስዕለት ተሳለች፡፡ ሐና የመጽነሷ ነገር ሲሰማም ቤተ ዘመዶቿ መጥተው ጎበኗት፡፡ አንድ አይኗ የማያይ ዘመድ ነበረቻት፣ ሐና እግዚአብሔር ያደረገልሽ ይህ ድንቅ ነገር ምንድነው ብላ ማሕጸኗን በዳሰሰችበት እጇ አይኗን ብትነካው በርቶላታል፡፡

ይህን አብነት አድርገው ሕሙማን እየመጡ ይፈወሱ ነበር፡፡ አይሁድም የእነዚህ ወገን ዳዊትና ሰሎሞን አርባ፣ አርባ ቀጥቅጠው ገዙን አሁን ደግሞ ከዚህች የሚወለድ ሊገዛን ነውን? በድንጋይ ወግረን እንግደላት ብለው ተነሱ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም ኢያቄምን ወደ ሊባኖስ ተራራ ይዘሀት ሽሽ ብሎት በዚያ ሳሉ ግንቦት 1 ቀን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዳለች፡፡ በድንጋጤና በጥድፊያ ሲወጣ ከያዘው ስንዴ በስተቀር የሚያቀርብላት ምግብ አልነበረውምና ንፍሮ ቀቅሎ፣ ቂጣ ጋግሮ አቅርቦላታል፡፡ በልደታ ቀን ንፍሮና ቂጣ የምንበላው ይህን አብነት አድርገን ነው፡፡ ገዳማውያን ዓለምን ትተው፣ ከምግብ ርቀው ለነፍሳቸው ሲገዙ እርሷን ተስፋ አድርገው ነውና ጸሎታቸውን ፈጥና ታሳርጋለች፡፡ በስሟ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸናም ትባርከናለች፡፡

ገዳማዊያኑን በመደገፍ ለነፍሳችን ስንቅን እንያዝ።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ኢትዮ ቴሌኮም ይፋ ያደረገው " ዘመን ገበያ " እንዴት ነው የሚሰራው ?*****************ዘመን የኦንላይን የገበያ ፕላትፎርም የቀረበው በቴሌ ብር ሱፐር አፕ ላይ ሲሆን ደንበኞች ከአ...
05/08/2025

ኢትዮ ቴሌኮም ይፋ ያደረገው " ዘመን ገበያ " እንዴት ነው የሚሰራው ?

*****************

ዘመን የኦንላይን የገበያ ፕላትፎርም የቀረበው በቴሌ ብር ሱፐር አፕ ላይ ሲሆን ደንበኞች ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ የሚፈልጉትን ምርት መገበያየት ይችላሉ።

የሸመቷቸውን ምርቶች ከነገ ጀምሮ መቀበል ይጀምራሉ ተብሏል።

ሸማቾች የሚፈልጉትን ምርት ከመረጡ በኋላ ምርቱን መቀበል የሚፈልጉበትን ቦታ በማስገባት ክፍያውን በቀጥታ በቴሌብር ይፈጽማሉ።

ነጋዴዎች ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ተጨማሪ አካውንት መክፈት ሳይጠበቅባቸው ቨርችዋል ስቶር ክሬት በማድረግ መጠቀም ይችላሉ።

የምርቶቹን ግዢ ሸማቾች ካከናወኑ በኋላ የትራንስፖርት ወጪውን አብረው የሚከፍሉ ሲሆን ምርቶቹን የማሸግ ሥራ ምርቱን ያቀረበው አካል / ነጋዴ የሚሰራ ይሆናል።

ምርቶቹን ከአቅራቢው / ነጋዴዎች ተቀብሎ በደንበኞች አድራሻ የማድረሱን ስራ ኢትዮ ቴሌኮም ይወጣል ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ...
05/07/2025

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል ክስ ቀረበባቸው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው በዚህ የክስ መዝገብ ክስ፤ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ፣ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን “ሀሰተኛ ታሪኳ ተሰራጭቷል” የተባለችው ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ ስድስት ተጠርጣሪዎች በሽብር ወንጀል ተከስሰዋል።

በአጠቃላይ 16 ተከሳሾች የተካተቱበትን የክስ መዝገብ፤ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 28፤ 2017 ያቀረበው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ነው። ከተከሳሾቹ መካከል ስምንቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቢሮ እና በወረዳ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ናቸው።

ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው መዝገብ ሶስት የክስ አይነቶች ጠቅሷል። የመጀመሪያው ክስ፤ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በ2011 ዓ.ም. የወጣን አዋጅ በመተላለፍ የቀረበ ነው። ዐቃቤ ህግ በክሱ የጠቀሰው የአዋጁ ድንጋጌ፤ “የሽብር ድርጊት” በመፈጸም “የሰው ህይወትን ለአደጋ ማጋለጥን” ይመለከታል።

ይህ ድንጋጌ ተጠቅሶ ክስ ከቀረበባቸው ተጠርጣሪዎች ውስጥ በቀዳሚነት የተቀመጡት በአሁኑ ወቅት ነዋሪነታቸውን በውጭ ሃገር ያደረጉት ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ተስፋዬ ወልደስላሴ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 14፤ የሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ካሳሁን ኃይሌ እና በዚሁ ወረዳ የስራ ስምሪት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋለልኝ አለማየሁ በመጀመሪያው ክስ የተካተቱ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ናቸው።

መረጃዉ
ethiopiainsider

" የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ያልያዘ አሽከርካሪ ማሽከርከር አይችልም " - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርየትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ፥ " ከያዝነው ዓመት ጀምሮ በሀገር አቀፍ...
05/07/2025

" የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ያልያዘ አሽከርካሪ ማሽከርከር አይችልም " - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ፥ " ከያዝነው ዓመት ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የአሽከርካሪዎች የሙያ ብቃት ምዘና ይጀመራል " ሲል አሳወቀ።

የብቃት ምዘናውን መስጠት ያስፈለገው 83 በመቶ በሀገሪቱ እየደረሰ የሚገኘው የትራፊክ አደጋ ከአሽከርካሪዎች እና ተሽከርካሪዎች ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ነው ብሏል።

ይህን ተከትሎም በዚህ ዓመት ምዘናው ሥራ ላይ ባሉ አሽከርካሪዎች እንደሚጀመር አረጋግጧል።

በዚሁ መሠረት በሕዝብ እና ደረቅ ጭነት ከ1 እስከ 3 ባሉ ደረጃዎች እንዲሁም ለፈሳሽ 1 እና 2 አሽከርካሪዎች የሙያ ብቃት ምዘና እንደሚሰጥ ተገልጿል።

የሙያ ብቃት ምዘና ከመሰጠቱ በፊት ለአሽከርካሪዎቹ የሙያ ስልጠና ይሰጣቸዋል ተብሏል።

ከስልጠናው በኋላ የሙያ ብቃት ምዘና (ሲኦሲ) እንደሚወስዱ እና ፈተናውን ያለፉት መንጃ ፈቃዳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንደሚኖረው ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በሌላ በኩል የሙያ ብቃት ምዘና ፈተናውን ወስደው ያላለፉ አሽከርካሪዎች እንደገና ስልጠና ወስደው ድጋሚ ይፈተናሉ ብሏል።

የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ያልያዘ አሽከርካሪ ማሽከርከር እንደማይችልም አሳውቋል።

በቀጣይም የሙያ ብቃት ምዘናው ታክሲን ጨምሮ በሌሎቹም አሽከርካሪዎች ላይ ይተገበራል ተብሏል።

መረጃው Tikvah Ethiopia

" በአሰቃቂ ሁኔታ ነው ዶርም ውስጥ በጩቤ ተወጋግቶ የተገደለው " - ተማሪዎች************************➡️ " ሕይወቱን ለማትረፍ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ ቀርቷል። ጥቃት አድራሹ...
05/06/2025

" በአሰቃቂ ሁኔታ ነው ዶርም ውስጥ በጩቤ ተወጋግቶ የተገደለው " - ተማሪዎች

************************

➡️ " ሕይወቱን ለማትረፍ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ ቀርቷል። ጥቃት አድራሹ ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሏል " - ዩኒቨርሲቲው

የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ተማሪው ዶርም ውስጥ መገደሉን ተማሪዎች ገለጹ።

ዩኒቨርሲቲው ጥቃት አድራሹ ተማሪ እንደሆነና በቁጥጥር ስር እንደዋለ አሳውቋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የጫሞ ካምፓስ ተማሪዎች ፥ በጫሞ ካምፓስ ዛሬ ጠዋት ላይ ብሎክ 9 የወንዶች ዶርም ውስጥ አንድ ተማሪ በጩቤ ተወጋግቶ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉን ገልጸዋል።

ተማሪዎቹ " እዚህ ካምፓስ ውስጥ መወጋት የተለመደ ከሆነ ሰነባብቷል " ያሉ ሲሆን ዩኒቨርስቲው በግቢ ውስጥ የሚፈጸሙ ተግባራትን ስሙን ለመጠበቅ ሲል መሸፋፈን ትቶ ለተማሪዎቹ ደህንነት ዋስትና እንዲሰጥ አሳስበዋል።

ተማሪዎች ባለው ነገር ስጋት ላይ እንደወደቁና መፍትሔ እንዲሰጣቸው ፤ ደህንነታቸውም በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲረጋገጥ ጠይቀዋል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምን አለ ?

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪው ግድያ አረጋግጦ የሀዘን መግለጫ ዛሬ ምሽት አውጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው " የሥነ- ትምህርትና ሥነ-ባህርይ ሳይንስ ትምህርት ቤት የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል የ2ኛ አመት ተማሪ የሆነው ናትናኤል ፀጉ አሰፋ ከጓደኛው ጋር በተፈጠረ የግል ፀብ በደረሰበት ጥቃት ዛሬ ጠዋት ሚያዚያ 28 ቀን 2017 ዓ/ም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል " ብሏል።

" ሕይወቱን ለማትረፍ በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ በመቅረቱ ማምሻውን 12:30 ላይ ሕይወቱ አልፋል " ሲል ገልጿል።

ጥቃቱም ያደረሰው ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሎ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጾ የሕግ ሂደቱን በመከታተል ውሳኔውን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።

መረጃዉ
ቲክቫህ ኢትዮጵያ

ጄኔራል ታደሰ ወረደ የ100 ቀናት እቅዳቸውን ይፋ አደረጉ፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት የሆኑት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ በሚቀጥሉት 100 ቀናት ለማከናወን ያቀዷቸውን ስ...
05/04/2025

ጄኔራል ታደሰ ወረደ የ100 ቀናት እቅዳቸውን ይፋ አደረጉ፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት የሆኑት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ በሚቀጥሉት 100 ቀናት ለማከናወን ያቀዷቸውን ስራዎች የሚያሳይ ዝርዝር ዛሬ ይፋ አድርገዋል፡፡

በዚህ ዝርዝር በቀዳሚነት የተቀመጠው ተፈናቃዮችን ወደመኖሪያቸው መመለስና የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ማድረግ የሚለው ነው፡፡ በቀጣይነት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች መረጋጋትን ማስፈን፣ አስተዳደሩን አካታች ማድረግ፣ ለስራ ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣ የህዝብን ቅሬታ ሰምቶ መፍትሄ ማምጣትና ሁለት ጫፍ የረገጠውን የክልሉን ፖለቲካ መጠገን የሚሉ ይገኙበታል፡፡

እንዲሁም የክልሉን ህልውናና ደህንነት በሚወስኑ አጀንዳዎች ላይ መግባት ለመፍጠር የሚያስችል ህዝባዊ ኮንፈረንስ ማድረግ፣ የተከፋፈለውን ዲያስፖራ ማቀራረብ፣ በክልሉ የሰፈነውን ሌብነት፣ ዝርፊያና ወንጀል ለመከላከል መስራት፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታትና የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ከፌዴራል መንግስት ተቋማት ጋር በቅርበት መስራት የሚሉ ይገኙበታል፡፡

YT Link 🔗

https://youtu.be/zklBut-qsRE?si=x3XS3J2aVHm4ZSX3

Address

America
Washington D.C., DC
20001

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hasab Today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hasab Today:

Share