Hasab Today

Hasab Today HasabToday
(1)

የህሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ በአደራዳሪዎች የሚመራ የምክክር መድረክ እንዳይካሄድ እያገደ መሆ...
11/14/2025

የህሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ በአደራዳሪዎች የሚመራ የምክክር መድረክ እንዳይካሄድ እያገደ መሆኑን ከሰሱ።
ሊቀመንበሩ አክለውም፣ ህወሓትም ሆኑ ዓለም አቀፍ አደራዳሪዎቹ፣ እንዲህ አይነት የጋራ ውይይት እንዲካሄድ በተደጋጋሚ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
ዶ/ር ደብረጽዮን ይህንን ያሉት ለድርጅቱ ይፋዊ ሚዲያ 'ወይን' (Woyen) በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በፕሪቶሪያ ስምምነት እና በህወሓት ህጋዊ ሁኔታ (legal status of the TPLF) ዙሪያ ለሰጡት አስተያየትም ምላሽ ሰጥተዋል።
"አደራዳሪዎቹም ሆኑ እኛ [ህወሓት] ተገናኝተን በስምምነቱ አፈጻጸም ላይ መወያየት እንፈልጋለን" ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ህወሓት ጥያቄውን በተደጋጋሚ ማቅረቡንና አደራዳሪዎቹም ለውይይት መገፋፋታቸውን አስረድተዋል።
ነገር ግን፣ "በአደራዳሪዎች ፊት በሚደረግ ውይይት ላይ ለመሳተፍ 'እምቢ ያለው የፌደራል መንግስት ነው'" ሲሉ ዶ/ር ደብረጽዮን ወቅሰዋል።
ሊቀመንበሩ በዚሁ ቃለ መጠይቅ ላይ አደራዳሪ አካላትንም ተችተዋል። ስምምነቱ እንዲተገበር ከመወትወት እና ምክር ከመስጠት ባለፈ፣ በፌደራል መንግስት ላይ "በቂ ጫና እያደረጉ አይደለም" (failing to exert adequate pressure) ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
በተለይም የቀድሞው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሃመር [Mike Hammer]፣ ስምምነቱ እንዲተገበር ከፍተኛ ግፊት ያደርጉ እንደነበር አስታውሰው፣ ከሳቸው መውጣት በኋላ (ወይም ምትክ አለመመደቡ) "ግልጽ ክፍተት ታይቷል" ብለዋል።

#ዜና #ሰበር #ሰበርዜና #ሀሳብ

" ወንጀል ፈጻሚው በፈጸመው ወንጀል ልክ ተመሳሳይ የሆነ ፍርድ እንዲሰጠው እጠይቃለሁ " - የተማሪ ሊዛ ቤተሰብበደሴ ከተማ "ተደፍራና ተገድላ" ተገኘች የተባለችው በዘንድሮው አመት ለምርቃት ...
11/14/2025

" ወንጀል ፈጻሚው በፈጸመው ወንጀል ልክ ተመሳሳይ የሆነ ፍርድ እንዲሰጠው እጠይቃለሁ " - የተማሪ ሊዛ ቤተሰብ

በደሴ ከተማ "ተደፍራና ተገድላ" ተገኘች የተባለችው በዘንድሮው አመት ለምርቃት ስትጠበቅ የነበረችው የሦስተኛ አመት በኮሌጅ ተማሪ ሊዛ ደሳለ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የደሴ ከተማ ፓሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ጉዳዩ በምርመራ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም ገልጸውልን የነበሩ የፓሊስ አካል ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ደግሞ፣ " ሰውየው/ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውሏል። ቀጣዩ ሥራ ይቀጥላል " ብለዋል።

የድርጊቱን ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ስንጠይቃቸውም፣ " ከሳምንት በኋላ ሙሉ መግለጫ ጠብቁ፤ አሁን ብናብራራው የፍትህ ስርዓቱ ይበላሻል " ብለዋል።

" ምርመራው አልቆ የጨመረሻው ውጤት ሲደርስ ሙሉ ማብራሪያ ይሰጣል፤ በመካከል ላይ ካለ ግን ይባላሻል። ወንጀሉ የተፈጸመው ምሽት ላይ ስለሆነ ፓሊስ ጉዳዩን እስከሚጨርስ ድረስ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፤ የተጠርጣሪውን ፎቶ ራሱ አለጠፍንም " ነው ያሉት።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ በበኩሉ፣ የተቋቋመው የምርመራ ቡድን ባደረገው የክትትልና ማጣራት " ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ/ም ዋና ወንጀል ፈፃሚው በቁጥጥር ስር መዋሉን " ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ተማሪዋ " መስከረም 28/2018 ዓ/ም የእህቷን የተበላሸ ሞባይል ለማሰራት አምሽታ ወደ ጓደኛዋ ቤት ሰመሀል ዝናቡ ለማደር ስትሄድ ጭንቅላቷ አንገቷን ከኋላና ከፊት ድብደባ ተፈፅሞባት ወደ ሆስፒታል የሄደች ሲሆን ህይወቷ መትረፍ አለመቻሉ ይታወቃል " ሲልም አስታውሷል።

በተማሪ ሊዛ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ሰምታችኋል ? ፓሊስ አነጋግሯችሁ ነበር? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ የጠየቃቸው አንድ የተማሪዋ ቤተሰብ፣ ተጠርጣሪው መያዙንና ቀጣዩን ሂደት በተመለከተ ፓሊስ እንዳነጋገራቸው ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ እንባ ነው ያነባው፤ እኛ ቤተቦች ደግሞ ደም ነው ያለቀስነውና ወንጀሉን ፈጻሚው አካል በፈጸመው ወንጀል ልክ ተመሳሳይ የሆነ ፍርድ እንዲሰጠው እጠይቃለሁ " ሲሉም ቀጣዩ የፍርድ ሂደት ፍትሃዊ እንዲሆንላቸው ከወዲሁ አሳስበዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#ዜና #ሀሳብ #መረጃ #ሰበር #መንግስት #አስደንጋጭ

‎" በአደጋዉ የ6 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ8 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል " - ፖሊስ ‎➡️ ‎" አደጋው የደረሰዉ በአምላኮ ላይ በነበሩ አማኞች ላይ ነው። "‎‎በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ አስተ...
11/09/2025

‎" በአደጋዉ የ6 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ8 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል " - ፖሊስ

➡️ ‎" አደጋው የደረሰዉ በአምላኮ ላይ በነበሩ አማኞች ላይ ነው። "

‎በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ቱላ ክፍለ ከተማ ዶሬ ባፋኖ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በፍጥነት ሲጓዝ የነበረ ሲኖ ትራክ መንገድ ስቶ በአምልኮ ስርዓት ላይ በነበሩ ሰዎች ላይ በመዉደቅ ባስከተለው አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

‎የሰላዳ ቁጥሩ ኮድ 3 -89991 ኢት የሆነ ሲኖትራክ ከሀዋሳ ከተማ ወደ ዶሬባፋኖ በመጓዝ ላይ እያለ ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ ቱላ ክፍለ ከተማ ፊንጫ ቀበሌ በተለምዶ ቤተመንግስት ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ሲደርስ መንገድ ስቶ በመዉጣቱ በአምልኮ ላይ በነበሩ ሰዎች ላይ ወድቆ አደጋ ማድረሱን ረዳት ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ አስታዉቀዋል።

‎በአደጋዉ የ6 ሰዎች ህይወት ወዲያዉኑ ሲያልፍ በ3 ላይ ከባድ በ5 ሰዎች ደግሞ ቀላልና መጠነኛ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።

‎ጉዳት የደረሰባቸው 8 ሰዎች ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻልስት ሆስፒታል ተወስደዉ ሕክምና እየተደረገላቸዉ መሆኑንም ረዳት ኮምሽነር ግርማ ማቴዎስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ የብልት እና የዳሌ ፕላስቲክ ቀዶ ህክምና ላይ የሚሰራ ክሊኒክ ስራዉን ጀመረተቀማጭነቱን ቱርክ ሀገር ያደረገው ኤስቴቲክ ኢንተርናሽናል ክሊኒክ በስነ ውበት ሕክምና ላይ በበርካታ ሀገ...
10/28/2025

በኢትዮጵያ የብልት እና የዳሌ ፕላስቲክ ቀዶ ህክምና ላይ የሚሰራ ክሊኒክ ስራዉን ጀመረ

ተቀማጭነቱን ቱርክ ሀገር ያደረገው ኤስቴቲክ ኢንተርናሽናል ክሊኒክ በስነ ውበት ሕክምና ላይ በበርካታ ሀገራት ላይ የሰራ ክሊኒክ ነው።

በተለያዩ ሀገራት ካሉት ስምንት ቅርንጫፎች በተጨማሪ ዘጠነኛውን ቅርንጫፍ በኢትዮጵያ መክፈቱ የክሊኒኩ ህዝብ ግንኙነት የሆኑት አቶ ተሾመ አወቀ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።

አቮራ ቢዝነስ ግሩፕ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኀበር በስነውበት ሕክምና በተለይም በፕላስቲክ ሰርጀሪ ዘርፍ ተጠቃሽ ከሆኑት የሕክምና ተቋማት አንዱ የሆነውን ኤስቴቲክ ኢንተርናሽናል ክሊኒክ በኢትዮጵያ በፍራንቻይዝ መክፈቱ ተገልጿል።

ክሊኒኩ ለ26 አመታትን በፕላስቲክ ሰርጀሪ ህክምና እየሰራ የቆየ ነው። ከሚሰጣቸው የፕላስቲክ ሰርጀሪ ህክምና መካከል የብልት፣ የመቀመጫ፣ የደረት፣ የጸጉር፣ የፊት እና በተለያዩ አደጋዎች ምክንያት የሚያጋጥሙ ችግሮች ላይ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

❗️ኢትዮጵያ አሁን ላይ እዳዋን ለመክፈል ምንም ችግር የለባትም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ×××××××××××××××××6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደ...
10/28/2025

❗️ኢትዮጵያ አሁን ላይ እዳዋን ለመክፈል ምንም ችግር የለባትም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

×××××××××××××××××

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በሪፎርሙ አመካኝነት ከ4 አስከ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የእዳ ሽግሽግ ተደርጓል ብለዋል፡፡

“ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግሥት አንድም ዶላር የንግድ ብድር አልወሰደም። ይህም እዳን ለመቆጣጠር ያለንን ጽኑ አቋም ያሳያል” ሲሉም አክለዋል፡፡

06/13/2025

የእስራኤል ጥቃት ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ?

  📈እስራኤል በኢራን ላይ ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከሰነዘረች በኋላ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 13 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ከ2020 በኋላ በቀን ውስጥ በዚህ ደረጃ ሲጨምር ከፍተኛው ነው ተብሏል።አሁ...
06/13/2025

📈

እስራኤል በኢራን ላይ ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከሰነዘረች በኋላ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 13 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

ከ2020 በኋላ በቀን ውስጥ በዚህ ደረጃ ሲጨምር ከፍተኛው ነው ተብሏል።

አሁን ያለው ውጥረት በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ መቆራረጥ እንዳይፈጥር ተሰግቷል።

በጥቃቱ መክንያት በዓለም ገቢያ ፈጣን እርምጃዎች እየተስተዋሉ ነው። የአክሲዮን ገቢያዎች ተዳክመዋል፤ ባለሀብቶች እንደ ወርቅ፣ ስዊስ ፍራንክ እና የጃፓን የን ያሉ ደህንነታቸው የተጠበቀ ወደሆኑ ንብረቶች እየተጣደፉ ነው።

ተንታኞች ውጥረቱ ተባብሶ በዚሁ ከቀጠለ ሁኔታው ​​የዓለምን የኃይል ገበያ የበለጠ ሊያናጋ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

ቀጣዮቹ 72 ሰዓታት ይህ ዋጋ በዚሁ ለመቀጠሉ ወይም ለመባሱ ወሳኝ ሰዓታት ናቸው ተብሏል።

ኢራን በቀን እስከ 3.3 ሚሊዮን በርሜል ታወጣለች፣ ይህም ከዓለም አቀፍ አቅርቦተለ 3 በመቶውን ይሸፍናል።

Source: BBC , CNBC
#ኢራን 🇮🇷

ቅድስት ድንግል ማርያም የልባችሁን መልካም መሻት ትሙላላችሁ !እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዐል አደረሳችሁ"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም። በህግ...
05/09/2025

ቅድስት ድንግል ማርያም የልባችሁን መልካም መሻት ትሙላላችሁ !

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዐል አደረሳችሁ

"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም። በህግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።" ይላል ታላቁ ሊቅ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም፡፡ ግንቦት አንድ ቀን በሊባኖስ ተራራ ላይ የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 86፡1-7 “መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡” በማለት አስቀድሞ ትንቢት ተናግሮላታል፡፡ “የተቀደሱ ተራሮች” ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ትንቢቱንና የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ “እመቤታችን በአባቷ ከንጉሡ ከዳዊት፤ በእናቷም ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው” ብላ ታስተምራለች፡፡ የእመቤታችን የቅድስት ማርያም ልደት ከሰው ሁሉ ልደት ይልቅ የከበረ ለአምላክ ሰው መሆን፣ ለተስፋው ቃል መፈጸም መንገድ የጠረገ ነው፡፡

ከዐበይት ነቢያት የሚቆጠረው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ “ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡” በማለት በ11÷1 ምዕራፍ ይናገራል፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም አበባ የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት የተናገረው ትንቢት “ከዕሴይ ስር ትወጣለች” ያላት አበባን የምታስገኝ በትር፣ አምላክ ሰው የሆነባት፣ ድንቅ የተዋሕዶ ምሥጢር የተፈጸመባት በግንቦት አንድ ቀን የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። እመቤታችን ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷ ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ።

በጊዜው ካህናቱ የመካኖችን መብዓ አይቀበሉም ነበርና፣ ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘን እንዲያርቅላቸው በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽመው ይማልዱ ነበርና የልባቸውን መሻት ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡ በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረዶ የመልአኩን ብስራት ለቅድስት ሐናም ነገራት። እርሷም ቃሉ እውነት እንደሆነ አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች፤ ሴትም ወንድም ብትወልድ በዘመናቸው ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ልታደርግ ስዕለት ተሳለች፡፡ ሐና የመጽነሷ ነገር ሲሰማም ቤተ ዘመዶቿ መጥተው ጎበኗት፡፡ አንድ አይኗ የማያይ ዘመድ ነበረቻት፣ ሐና እግዚአብሔር ያደረገልሽ ይህ ድንቅ ነገር ምንድነው ብላ ማሕጸኗን በዳሰሰችበት እጇ አይኗን ብትነካው በርቶላታል፡፡

ይህን አብነት አድርገው ሕሙማን እየመጡ ይፈወሱ ነበር፡፡ አይሁድም የእነዚህ ወገን ዳዊትና ሰሎሞን አርባ፣ አርባ ቀጥቅጠው ገዙን አሁን ደግሞ ከዚህች የሚወለድ ሊገዛን ነውን? በድንጋይ ወግረን እንግደላት ብለው ተነሱ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም ኢያቄምን ወደ ሊባኖስ ተራራ ይዘሀት ሽሽ ብሎት በዚያ ሳሉ ግንቦት 1 ቀን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዳለች፡፡ በድንጋጤና በጥድፊያ ሲወጣ ከያዘው ስንዴ በስተቀር የሚያቀርብላት ምግብ አልነበረውምና ንፍሮ ቀቅሎ፣ ቂጣ ጋግሮ አቅርቦላታል፡፡ በልደታ ቀን ንፍሮና ቂጣ የምንበላው ይህን አብነት አድርገን ነው፡፡ ገዳማውያን ዓለምን ትተው፣ ከምግብ ርቀው ለነፍሳቸው ሲገዙ እርሷን ተስፋ አድርገው ነውና ጸሎታቸውን ፈጥና ታሳርጋለች፡፡ በስሟ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸናም ትባርከናለች፡፡

ገዳማዊያኑን በመደገፍ ለነፍሳችን ስንቅን እንያዝ።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ኢትዮ ቴሌኮም ይፋ ያደረገው " ዘመን ገበያ " እንዴት ነው የሚሰራው ?*****************ዘመን የኦንላይን የገበያ ፕላትፎርም የቀረበው በቴሌ ብር ሱፐር አፕ ላይ ሲሆን ደንበኞች ከአ...
05/08/2025

ኢትዮ ቴሌኮም ይፋ ያደረገው " ዘመን ገበያ " እንዴት ነው የሚሰራው ?

*****************

ዘመን የኦንላይን የገበያ ፕላትፎርም የቀረበው በቴሌ ብር ሱፐር አፕ ላይ ሲሆን ደንበኞች ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ የሚፈልጉትን ምርት መገበያየት ይችላሉ።

የሸመቷቸውን ምርቶች ከነገ ጀምሮ መቀበል ይጀምራሉ ተብሏል።

ሸማቾች የሚፈልጉትን ምርት ከመረጡ በኋላ ምርቱን መቀበል የሚፈልጉበትን ቦታ በማስገባት ክፍያውን በቀጥታ በቴሌብር ይፈጽማሉ።

ነጋዴዎች ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ተጨማሪ አካውንት መክፈት ሳይጠበቅባቸው ቨርችዋል ስቶር ክሬት በማድረግ መጠቀም ይችላሉ።

የምርቶቹን ግዢ ሸማቾች ካከናወኑ በኋላ የትራንስፖርት ወጪውን አብረው የሚከፍሉ ሲሆን ምርቶቹን የማሸግ ሥራ ምርቱን ያቀረበው አካል / ነጋዴ የሚሰራ ይሆናል።

ምርቶቹን ከአቅራቢው / ነጋዴዎች ተቀብሎ በደንበኞች አድራሻ የማድረሱን ስራ ኢትዮ ቴሌኮም ይወጣል ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ...
05/07/2025

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል ክስ ቀረበባቸው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው በዚህ የክስ መዝገብ ክስ፤ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ፣ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን “ሀሰተኛ ታሪኳ ተሰራጭቷል” የተባለችው ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ ስድስት ተጠርጣሪዎች በሽብር ወንጀል ተከስሰዋል።

በአጠቃላይ 16 ተከሳሾች የተካተቱበትን የክስ መዝገብ፤ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 28፤ 2017 ያቀረበው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ነው። ከተከሳሾቹ መካከል ስምንቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቢሮ እና በወረዳ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ናቸው።

ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው መዝገብ ሶስት የክስ አይነቶች ጠቅሷል። የመጀመሪያው ክስ፤ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በ2011 ዓ.ም. የወጣን አዋጅ በመተላለፍ የቀረበ ነው። ዐቃቤ ህግ በክሱ የጠቀሰው የአዋጁ ድንጋጌ፤ “የሽብር ድርጊት” በመፈጸም “የሰው ህይወትን ለአደጋ ማጋለጥን” ይመለከታል።

ይህ ድንጋጌ ተጠቅሶ ክስ ከቀረበባቸው ተጠርጣሪዎች ውስጥ በቀዳሚነት የተቀመጡት በአሁኑ ወቅት ነዋሪነታቸውን በውጭ ሃገር ያደረጉት ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ተስፋዬ ወልደስላሴ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 14፤ የሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ካሳሁን ኃይሌ እና በዚሁ ወረዳ የስራ ስምሪት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋለልኝ አለማየሁ በመጀመሪያው ክስ የተካተቱ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ናቸው።

መረጃዉ
ethiopiainsider

Address

America
Washington D.C., DC
20001

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hasab Today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hasab Today:

Share