Hasab Today

Hasab Today HasabToday
(1)

06/06/2026

Hasab Today

ዋልያዎቹ በድል ተመልሰዋል! 🇪🇹⚽️

ዛሬ ቅዳሜ በድሬዳዋ ስታዲየም በተደረገው አስደናቂ የወዳጅነት ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማላዊን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ለዋልያዎቹ የድል ጎሏን ያስቆጠረው ፍፁም ጥላሁን ሲሆን፣ ይህ ውጤት ለቀጣይ ትልልቅ ውድድሮች ለሚያደርጉት ዝግጅት ትልቅ መነቃቃትን ፈጥሯል።

የሁለቱ ቡድኖች ወሳኝ የሁለተኛ ዙር ጨዋታ በሚቀጥለው ማክሰኞ ይካሄዳል። ዋልያዎቹ ድላቸውን ይደግሙታል? 🦅🔥

06/06/2026

Hasab Today

"በጥሩ ብቃቴ ላይ እያለሁ ላሚን ያማልን ኪሴ ውስጥ ነው የማስገባው" — ፓትሪስ ኤቭራ 👀🗣️

"በአሪፉ የብቃት ዘመኔ ከያማል ጋር ብንገጠም ኖሮ፣ በቁሜ ነበር የምበላው። ላሚን ይቅርታ አድርግልኝ... እወድሃለሁ...ነገር ግን ክሪስቲያኖን ጠይቅ፣ ሜሲን ጠይቅ፣ እኔን የገጠሙ ሌሎችንም ተጫዋቾች ጠይቅ፤ ሜዳ ላይ እኔ ጥሩ ጓደኛ አይደለሁም።"

#የኳስወሬ #የአውሮፓእግርኳስ #ማንቼ #ባርሴሎና #እግርኳስ #ስፖርት #ፓትሪስኤቭራ #ላሚንያማል

Hasab Sports     "የአርሲው ጥቃት በሸኔ እና በፋኖ ታጣቂዎች ትብብር የተፈጸመ ነው" — ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨  የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በ...
06/06/2026

Hasab Sports

"የአርሲው ጥቃት በሸኔ እና በፋኖ ታጣቂዎች ትብብር የተፈጸመ ነው" — ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባወጣው መግለጫ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጥቃቱ የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል።

ይህ ጥቃት የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ አማፂያን እና ከውጭ ኃይሎች ጋር በቅንጅት የተፈጸመ ነው ብለዋል። ዋና ዓላማውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትን መፍጠር እና ምርጫን ማስተጓጎል እንደነበር ጠቁመዋል።

ዋና ዋና ነጥቦች፦

የጥፋት ኃይሎች ቁርኝት፦ የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል። ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወንም ሰፊ ርብርብ አድርገዋል።

የታጣቂዎቹ መናበብ፦

በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ቡድን ከፋኖ ታጣቂዎች ጋር በመናበብ መንገዶችን ለመዝጋት ሞክሯል። ሆኖም በጸጥታ ኃይሉ እርምጃ ፍላጎቱ ከሽፏል።

ስስ ዒላማዎች፦ ቡድኑ የጸጥታ ኃይሉን መቋቋም ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ አተኩሯል። በአርሲ ዞን አሰኮ አካባቢ ጥቃት በመፈጸም የሃይማኖትና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ ሞክሯል።

በአሁኑ ወቅት የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደበት ይገኛል።

የመንግሥት ምላሽ፦ መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት እየተከታተለ ነው። በጥቃቶች አማካኝነት ፍርሃትና ክፍፍል ለመፍጠር የተወጠነው እኩይ ተግባር በደኅንነት መዋቅሩ ተስተጓጉሏል።የጋራ ውግዘት ጥሪ፦ ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ ሊወገዙ ይገባል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የፖለቲካ ቅሬታዎች መፍትሔ ማግኘት ያለባቸው በሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደቱ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት ብቻ እንደሆነ አሳስበዋል።

ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትሰላም ለኢትዮጵያ! ሰላም ለሕዝባችን!(ወሎ አዲስ የሕዝብ አድማስ)

የHasab Today መጠይቅ ፦ በተነሳው ሐሳብ ላይ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው? ይስማማሉ?

#ሀሳብ

"ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት ከሽፏል"- የሰላም ሚኒስቴር ***በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማደፍረስ ጽንፈኛ ኃይሎችና የውጭ ጠላቶች ...
06/06/2026

"ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት ከሽፏል"
- የሰላም ሚኒስቴር
***

በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማደፍረስ ጽንፈኛ ኃይሎችና የውጭ ጠላቶች የከፈቱት ሁለንተናዊ ጥቃት መክሸፉን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ሀገራዊ ለውጡን የማይቀበሉ አካላት በመሬት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ከመፈጸም ጀምሮ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፕሮፓጋንዳና የሥነ-ልቦና ጦርነት ሲያካሂዱ ቆይተዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ምርጫውን የህልውና እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ በአንጻሩ የስልጣን ሽግግርን በድምጽ መስጫ ኮሮጆ ሳይሆን በኃይል ለመጠቅለል የሚሹ የውስጥ ቅጥረኞችና የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ሂደቱን ለማስቆም ከምርጫው በፊት፣ ወቅትና በኋላ ከፍተኛ ሴራዎችን መሸረባቸውን ይፋ አድርጓል።

አፍራሽ ኃይሎቹ የመንግሥትን ሕጋዊ ቅቡልነት ለማሳጣትና ኢትዮጵያን ወደ ሥርዓት አልበኝነት ለመክተት ሕዝቡ የምርጫ ካርድ እንዳይወስድ፣ በፖለቲካ ድጋፍ ሰልፎች ላይ እንዳይገኝ እና በምርጫው ቀን ድምጽ እንዳይሰጥ ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር ተጠቅሷል።

ሆኖም የኢትዮጵያ ህሕብ ለጥሪዎቻቸው እውቅና ባለመስጠትና የጽንፈኝነትን አጀንዳ ውድቅ በማድረግ፥ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ተሳትፎ የምርጫ ካርድ በመውሰድ፣ በሰልፎች ላይ በነጻነት በመገኘትና በምርጫው ቀን በነቂስ ወጥቶ ድምጽ በመስጠት አፍራሽ ኃይሎቹን ማሸነፉን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ይህ የዲሞክራሲ ስኬት ያለመስዋዕትነት እንዳልመጣ የጠቀሰው የሰላም ሚኒስቴር፤ የጸጥታ ተቋማት ባደረጉት ወቅቱን የጠበቀና የተቀናጀ አጸፋዊ እርምጃ የሽብር ዕቅዶቹ ሊከሽፉ መቻላቸውን አስታውቋል።

ሆኖም የሕዝቡን አብሮነት ለመስበር የተሞከሩ የሽብር ጥቃቶች እንደነበሩ ጠቅሶ፤ ህዝቡ የከፈለው መስዋዕትነት ጽንፈኝነትን በመቃወም ሀገርን የሚያስቀጥል ሕጋዊ መንግሥት ለመመስረት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳየበት መሆኑም ተመላክቷል።

IMF ለኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ የሚያስገኝ የስምምነት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀየዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ ...
06/05/2026

IMF ለኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ የሚያስገኝ የስምምነት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።

ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።

በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።

የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።

እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።

ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።

ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።

የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።

ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦

• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።

• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።

የውጭ ዕዳ ሽግሽግ

የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።

የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።

ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።

  በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ምዕመናን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን እንዲሁም ዝርፊያ መፈጸሙን ሀገረ ስብከቱ ማሳወቁ ...
06/05/2026



በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ምዕመናን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን እንዲሁም ዝርፊያ መፈጸሙን ሀገረ ስብከቱ ማሳወቁ ይታወሳል።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች የሟቾች ቁጥር 15 መሆኑንና አስክሬናቸው ያልተነሳ ሰዎች መኖራቸውን ገልጸው ነበር።

አሁን ላይ ሁኔታውን በተመለከተ ነዋሪዎቹ በሰጡት ቃል ፥ የት እንዳሉ ያልታወቀ የጠፉ ሰዎች ስለመኖራቸው እንዲሁም ተፈናቃዮች በችግር ላይ ስለመሆናቸው ገልጸዋል።

" የጠፉ፣ በትክክል አስክሬናቸው ያልተነሳ ምን ያህል እንደሆኑ ለመግለጽ አሁን ላይ አንደማይችሉ " ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ፥ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል፥ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመው ንፁሃን መገደላቸውን አረጋግጠዋል። ምን ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ግን አልገለጹም።

ኃላፊው፣ በቤተክርስቲያን ላይም ያነጣጠረ ጥቃት መፈጸሙንም ያመለከቱ ሲሆን ይህን ሁሉ ያደረገው " የሸኔ ሽብርተኛ ቡድን ነው " ብለዋል። ምክንያቱ ደግሞ የግንቦት 24 ምርጫን ለማደናቀፍ እንደሆነ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

" ቡድኑ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ተልዕኮ ወስዶ ስምሪት ሰጥቶ ነው ምርጫውን ለማደናቀፍ የተንቀሳቀሰው ፤ ሃይማኖት እና ብሄርም የለየ አይደለም " ሲሉም አቶ ኃይሉ አዱኛ ገልጸዋል።

በዚህ አካባቢ ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ጥቃቶች ተፈጽመው በርካታ ንፁሃን መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን ከአካባቢውና ክልሉ ጭምር ማብራሪያ ለማግኘት የሚደረገው ጥረት አይሳካም ነበር።

ከወራት በፊት በዚሁ ዞን በርካታ ምዕመናን መገደላቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ልዑካን ልኮ ማጣሪያ ካደረገ በኋላ፣ " ግድያው ሃይማኖት እና ብሄርን ትኩረት ያደረገ አይደለም " የሚል ሪፖርት ማቅረቡ ይታወሳል።

ይህ ሪፖርት ወጥቶ ብዙም ሳይቆይ ዳግም በምእመናን ላይ ጥቃት መፈጸሙን ሀገረ ስብከቱ አሳውቆ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።

የአሁኑ ጥቃት ከወራት በፊት ከነበረው ተከታታይ ጥቃት፣ ግድያና እገታ በኋላ የተፈጸመ ሲሆን የክልሉ መንግሥት ድርጊቱን የፈጸመው " ሸኔ " እንደሆነና ምርጫ ለማደናቀፍ እንደሆነ አመልክቷል።

እስካሁን ባለው ሁኔታ በአካባቢው ከሚፈጸሙ ጥቃቶች ጋር በተያያዘ ምርመራ ተደርጎ ለህዝብ ይፋ ሲደረግ፣ የድርጊቱ ፈጻሚዎች ለፍርድ ሲቀርቡና ፍትህ አደባባይ ላይ ሲቆሙ ፣ ዜጎችን ለመጠበቅ የተሳናቸው አካላት ተጠያቂ ሲሆኑ አልታየም። ወይም " ገዳዮች ተይዘው በዚህ ፍርድ ቤት ጉዳያቸው እየታየ ነው " ሲባል አይሰማም።

Hasab Sports  Hasab Today 🛑 "እስከ መቼ?" —   በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት ዙሪያ ያስተላለፉት አስቸኳይ አባታዊ መልእክት Hasab Todayግንቦት ...
06/04/2026

Hasab Sports
Hasab Today

🛑 "እስከ መቼ?" — በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት ዙሪያ ያስተላለፉት አስቸኳይ አባታዊ መልእክት

Hasab Today

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.

አዲስ አበባ፣ #ኢትዮጵያ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያንና በምእመናን ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ጥቃት በማስመልከት ጥልቅ ኀዘን የተሞላበት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል።

የቅዱስነታቸው ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ሰፍሯል፦

📋 የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ሙሉ መልእክት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

"ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።"

(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።

የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት፣ ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

⚠️ ለመንግሥትና ለጸጥታ አካላት የተላለፈ ጥሪ

ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ፤ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ኃላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነው፤ በመሆኑም፦

ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በአስቸኳይ እንድታስቆሙ፣

ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

🤝 ለምእመናንና ለመላው ኢትዮጵያውያን የተላለፈ ጥሪ

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

🕊️ ማጠቃለያ ጸሎትና ቡራኬ

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ፤ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እንተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!

አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ

ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ

ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ምንጭ፦ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

#ሀሳብቱደይ

  Hasab Sports    ጌዴኦ ዞን፡ ሊያገባ ጥቂት ቀናት በቀሩት ወጣት ላይ አሰቃቂ ግድያ በፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ ተፈረደበት !፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የጌዴኦ ዞን ...
06/04/2026


Hasab Sports



ጌዴኦ ዞን፡ ሊያገባ ጥቂት ቀናት በቀሩት ወጣት
ላይ አሰቃቂ ግድያ በፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ ተፈረደበት !

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ "የቀድሞ ፍቅረኛዬን ልታገባ ነው" በሚል በቀል በአንድ ወጣት ላይ አሰቃቂ ግድያ በፈጸመው ፀጋዬ ታደሰ ላይ የመጨረሻ የሞት ፍርድ ውሳኔ ማስተላለፉን የዞኑ ፖሊስ እና ዓቃቤ ሕግ መምሪያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

የወንጀሉ ዝርዝር መነሻ

የተፈጸመበት ቀንና ቦታ፦ ወንጀሉ የተፈጸመው ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በገደብ ከተማ ነው።

የተጎጂው ማንነት፦ ሟች ወጣት ተመስገን ዳንኤል ይባላል፤ የአቢሲኒያ ባንክ ባልደረባ የነበረ ሲሆን ጋብቻውን ለመፈጸም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውት ነበር።

የወንጀሉ አፈጻጸም፦ ተከሳሹ ፀጋዬ ታደሰ (የሟች እጮኛ የቀድሞ ፍቅረኛ) ግድያውን የፈጸመው በቂምና በበቀል ተገፋፍቶ ለረጅም ጊዜ አቅዶበት ነው። በመጀመሪያ ወጣት ተመስገንን በሽጉጥ ለመግደል የሞከረ ቢሆንም ሽጉጡ በመክሸፉ፣ በስለት ደጋግሞ በመውጋት በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል።

የፍርድ ቤት ውሎ እና የውሳኔ ሂደት

የማስረጃ አቀራረብ፦ ተከሳሹ ፍርድ ቤት ቀርቦ የተከሰሰበትን ወንጀል ክዶ በጠበቃ ቢከራከርም፣ ፖሊስና ዓቃቤ ሕግ ጠንካራ የሰውና የሕክምና ማስረጃዎችን በማቅረብ ወንጀሉን ማረጋገጥ ችለዋል። ተከሳሹ በበኩሉ ምንም ዓይነት የመከላከያ ምስክር ማቅረብ አልቻለም።

የቅጣት ውሳኔው ማረጋገጫ፦ ፍርድ ቤቱ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በነበረው ችሎት መነሻ ቅጣቱን ሞት በማድረግ፣ ለግንቦት 26 ቀን የሁለቱንም ወገን የቅጣት አስተያየት ለመስማት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።

የመጨረሻ ውሳኔ፦ ግንቦት 26 ቀን በዋለው ችሎት፣ ከተከሳሽ የቀረቡ ሁለት የቅጣት ማቅለያዎች እና ከዓቃቤ ሕግ የቀረቡ ሁለት ማክበጃዎች እርስ በርስ በመቻቻላቸው (በመጣጣማቸው) ፍርድ ቤቱ የሞት ቅጣቱን አጽድቋል።

ማጠቃለያ፦ ፍርድ ቤቱ የተላለፈውን የሞት ፍርድ ውሳኔ ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ለዲላ ማረሚያ ተቋም ትዕዛዝ ማስተላለፉን የዞኑ ፖሊስ እና ዓቃቤ ሕግ መምሪያዎች አረጋግጠዋል።

ምንጭ፦ ቲክቫህ ኢትዮጵያ (ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም)

#ሀሳብቱደይ

ኢራን በኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት በርካቶች መጎዳታቸው ተገለጸየኢራን ድሮኖች የኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ረቡዕ ማለዳ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎች መቋ...
06/03/2026

ኢራን በኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት በርካቶች መጎዳታቸው ተገለጸ

የኢራን ድሮኖች የኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ረቡዕ ማለዳ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎች መቋረጣቸው ተገለጸ።
በኩዌት የአውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት የተፈጸመው ቴህራን እና ዋሺንግተን አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ሲሆን በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውም ተገልጿል።

ሁለት የኢራን ዜና ወኪሎች ቴህራን የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር ማቋረጧን ማክሰኞ ዕለት ዘግበዋል።
ትራምፕ ግን ዘገባውን አጣጥለው ንግግሮች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋል።
የኩዌት መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳዑድ አብዱላዚዝ አል ኦታእቢ “በርካታ ጥቃት ፈጻሚ ድሮኖች” የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃን ዒላማ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።
በጥቃቱ የመንገደኞች ማስተናገጃው ክፉኛ መጎዳቱን የገለጹ ሲሆን “በርካታ ሰዎችን” አቁስሏል ብለዋል።

የአውሮፕላን ማረፊያው በኢራን ጦርነት ምክንያት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ከሁለት ቀናት በፊት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም. ነበር።
ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የአሜሪካ ጦር ኢራን በኩዌት እና ባህሬን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ጠቅሶ በወታደራዊ ተቋማቷ ላይ የአጸፋ ምላሽ ድብደባ ማካሄዱን አስታውቋል።
የአሜሪካ ጦር አክሎም በኩዌት የሚገኙ የጦር ሰፈሮቹን ዒላማ ያደረጉ “በርካታ ድሮኖችን መትተን ጥለናል” ሲል አስታውቋል።

የኢራን ፈጥኖ ደራሽ አብዮታዊ ዘብ በባህሬን የሚገኝ የአሜሪካ ባሕር ኃይል ዋና ማዘዣ እና ኩዌትን በስም ሳይጠቅስ ሌላ አገር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።
አክሎም ጥቃቱን የፈጸመው የአሜሪካ ጦር የጣለውን እገዳ ለማለፍ እየተንቀሳቀሰች የነበረች ነዳጅ ጫን መርከብ ሞተር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎመሆኑን ጠቅሷል።
አብዮታዊ ዘቡ በመግለጫው “ከዚህ በፊት ለማንኛውም ጥቃት የምንሰጠው ምላሽ የተለየ እና የከፋ እንደሚሆን ተናግረን በነበረው መሠረተ እረምጃውን ወስደናል” ብሏል።

06/03/2026



ሊቨርፑል አዲስ አሰልጣኙን መቼ ያሳውቃል ?

343Sports HT

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላን በአሰልጣኝነት ለመሾም ከስምምነት ደርሰዋል።

አሰልጣኙ በሊቨርፑል የሁለት አመት ኮንትራት ለመፈረም ቀጠሮ እንደተያዘላቸው ተነግሯል።

አንዶኒ ኢራኦላ ሊቨርፑልን የሚረከቡት እንደ ' ማናጀር ' ሳይሆን በዋና አሰልጣኝነት መሆኑን ዘ አትሌቲክ አረጋግጧል።

አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ የራሳቸውን የአሰልጣኞች ቡድን ይዘው ወደ ሊቨርፑል መምጣት ይፈልጋሉ ተብሏል።

ሊቨርፑል በሳምንቱ መጨረሻ ሐሙስ ወይም አርብ አዲሱን አሰልጣኝ በይፋ ለማስተዋወቅ ቀነ ቀጠሮ ይዘዋል።



Address

America
Washington D.C., DC
20001

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hasab Today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hasab Today:

Share