Enawra - ኑና እናውራ

Enawra - ኑና እናውራ The best online entertainment for Ethiopians

06/15/2025

ባህራን እንዲሞት ከተጣለበት ባህር በደህንነት ወጥቶ የመልካም ሰው ልጅ ሆኖ አደገ፣ ወደ ባህር የጣለውንም ሰው ሀብት ወርሶ የጠበቀው አባቱ ቅዱስ ሚካኤልን እየዘከረ በስሙ ለንዳያን እየመጸወተ፣ አቢያተ ክርስቲያናትን እያሳነጸ ኖረ።

ቅድስት አፎሚያ ባሏ አስተራኒቆ ሊያርፍ ሲል እንዲያደርግላት የለመነችው የመጨረሻው ነገርብየቅዱስ ሚካኤልን ስዕል በሰሌዳ እንዲያሰራላት ነው። በዚያ ስዕልም ዲያብሎስን ሁለት ጊዜ አሳፍራ መልሳዋለች። በመጨረሻም ያላትን ሁሉ ለነዳያንና ለቤተክርስቲያን ማሰሪያ ሰጥታ አርፋለች።

ታላቁ አለቃ ሺ በክንፉ፣ ሺ በአክናፉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ለወዳጆቹ ፈጥኖ ደራሽ ደግ አባት ነው። ውለታው የበዛላቸው እናቶቻችን ደግሞ በታቦታት ንግስ ጊዜ ፡-

"ቅዱስ ሚካኤል ለወደደው
ከእሳት ያወጣል ከነደደው!!!" እያሉ ይዘምሩለታል።

ዘማሪ አቤል መክብብም በጥዑም ዜማ

"በሔድኩበት ሁሉ ከአፌ አትነጠልም
የማር ወለላ ነው ሚካኣል ያንተ ስም!!!" ሲል ውለታውን ያወሳል።

"ማር ሚካኤል ልበል" አዲስ መዝሙር በቅርብ ቅን በማህቶት ቲዩብ።

06/14/2025

*አስደሳች የህይወቶ ቀናት በአዲሱ ኢንፊኒክስ HOT 50 ይደምቃል!*

በጥራቱ የተመሰከረለትን እና ለአያያዝ ምቹ ሆኖ የቀረበው አዲሱ ኢንፊኒክስ HOT 50 አንዴ ቻርጅ ተደርጎ ቀኑን ሙሉ አብሮት የሚቆይ ባትሪም አካቶ ይዞዋል። አዲሱን ኢንፊኒክስ HOT 50 ሲሸምቱ እና የሳፋሪኮም ሲም ካርድን ሲጠቀሙ ነፃ የ 5 GB የኢንተርኔት ፓኬጅ እና 1000 ደቂቃ የአየር ሰዓት አገልግሎት ከሌሎች አጓጊ ከሆኑ ሽልማቶች ጋር ይጠብቆታል።

06/14/2025

ረዳኤ ምንዱባን፣ ሰዳዴ ሳጥናኤል፣ ልዑለ መንበር ይሉታል ቅዱሳን አባቶቻችን።

ለወዳጆቹ ፈጥኖ ደራሽ ነው። ቅዱስ ሚካኤል ብለው የጠሩት በርካቶችን እንኳን ከታሰበ ከተወረወረ ታድጓል።

ሁሉም በየጸጋው በየጦታው ያስበዋል ይዘክረዋል። ልጆቻቸውን በስሙ "ተስፋ ሚካኤል፣ ገብረ ሚካኤል...." እያሉ የሚሰይሙ፣ ዝክሩን የሚዘክሩ ነዳያንን የሚመግቡ፣ አቢያተ ክርስቲያናትን የሚያሳንጹ፣ ሌሊትና ቀን በዝማሬ የሚያመሰግኑት በርካቶች ህልቆ መሳፍርት የላቸውም።

ዘማሪ አቤል መክብብም በአዲሱ ዝማሬው "ማር ሚካኤል ልበልህ" ይለዋል።

"ባርከህ ያሳድግከኝ በቅኔ በዜማ
መዝሙር አልሰስትም አባቴ ላንተማ!!!"

በቅርብ ቀን በማህቶት ቲዩብ ይጠብቁን።

06/10/2025

በሽልማት የሚንበሸበሹበት እድል ይዞሎት የመጣው ኢንፊኒክስ ሞባይል ኢትዮጵያ ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር አዲሱን ኢንፊኒክስ HOT 50 ስልኮችን አቅርቦሎታል። ለአያያዝ ምቹ እና በተለያዩ የከለር አማራጮች ያለው ሲሆን አንዴ ቻርጅ ተደርጎ ቀኑን ሙሉ አብሮት የሚቆይ ባትሪም አካቷል። አዲሱን HOT 50 ሲሸምቱ እና የሳፋሪኮም ሲም ካርድን ሲጠቀሙ ነፃ የ 5 GB የኢንተርኔት ፓኬጅ እና 1000 ደቂቃ የአየር ሰዓት አገልግሎት ከሌሎች አጓጊ ከሆኑ ሽልማቶች ጋር ይጠብቆታል። ሽልማቱ ለ3 ወር የሚቆይ ይሆናል!

ይምጡ ይሸምቱ በሽልማት ይንበሽበሹ!!

 ቴክኖ ካሞን 30 5G የሰጠን አስደናቂ ቴክኖሎጂዎች ሳያንስ የአለማችን የመጨረሻው የሆነውን የአምስተኛውን ትውልድ ፈጣን የኔትወርክ ቴክኖሎጂን 5Gን መጠቀም ያስችላል፡፡ ምን ይሄ ብቻ የቴክ...
06/09/2025



ቴክኖ ካሞን 30 5G የሰጠን አስደናቂ ቴክኖሎጂዎች ሳያንስ የአለማችን የመጨረሻው የሆነውን የአምስተኛውን ትውልድ ፈጣን የኔትወርክ ቴክኖሎጂን 5Gን መጠቀም ያስችላል፡፡ ምን ይሄ ብቻ የቴክኖ ካሞን 30 5Gን ሲሸምቱ 500 ብር የሞባይል ካርድ ላዩ ላይ ከኛ ይታከልበታል፡፡ ታዲያ ምን ይጠብቃሉ ዛሬውኑ ቴክኖ ካሞን 30 5Gን የርሶ ያድርጉ ከአለም እኩል ይራመዱ!!




 ፎቶ ተነስቼ ኤዲት ላርግ ቢሉ 50 ሜጋ ፒክስል ጥርት ያለ ካሜራ ፣ ማህበራዊ ሚዲያን ልጠቀም ቢሉ 6.78 ኢንች ስክሪን እና 120 ሀርዝ ፈጣን ስክሪን፣ ኮንቴንቶቼን ላጋራ ቢሉ ፈጣን 5G ...
06/05/2025



ፎቶ ተነስቼ ኤዲት ላርግ ቢሉ 50 ሜጋ ፒክስል ጥርት ያለ ካሜራ ፣ ማህበራዊ ሚዲያን ልጠቀም ቢሉ 6.78 ኢንች ስክሪን እና 120 ሀርዝ ፈጣን ስክሪን፣ ኮንቴንቶቼን ላጋራ ቢሉ ፈጣን 5G ኔትወርክ፣ በተለያዩ የከለር አማራጮች የቀረበ ቴክኖ ካሞን 30 5G ሁሉን በአንድ የሚያገኙበት፡፡ ቴክኖ ካሞን 30 5Gን ይሸምቱ በ500 ብር የሞባይል ካርድ ሽልማት ይንበሽበሹ፡፡




ለ38 ዓመታት ተበልቶ ዛሬም ሙሉ ነውከነገደ እሥራኤል የተገኘች ናት፤ የተወለደችው ኢየሩሳሌም ውስጥ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው፡፡ ወላጆቿ ክርስቲያኖች በመሆናቸው በሚገባው ፈሊጥ አሳድ...
06/05/2025

ለ38 ዓመታት ተበልቶ ዛሬም ሙሉ ነው

ከነገደ እሥራኤል የተገኘች ናት፤ የተወለደችው ኢየሩሳሌም ውስጥ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው፡፡ ወላጆቿ ክርስቲያኖች በመሆናቸው በሚገባው ፈሊጥ አሳድገው ወደ ትምሕርት አስገቧት፤ ቅድስት ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ፡፡ አስተማሪዋ ገዳማዊ መነኮስ ነበርና ከተማ ውስጥ አያድርም፡፡ አስተምሯት ዕለቱኑ ወደ በዓቱ ይመለስ ነበር እንጂ:: ዓመተ ክርስቶስ ብሉይ ከሐዲስ ጠንቅቃ ተማረች፡፡ አንድ ቀን እንደ ልማዷ ልትማር ብትጠብቀውም መምሕሯ ሊመጣ አልቻለም፡፡ ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ መነኮሱን ልትጠይቅ: አንድም ልትማር ወደ በዓቱ ሔደች፡፡ በሩ ላይ ደርሳ ብታንኳኳም መልስ አጣች፡፡ ከውስጥ ግን ምርር ያለ የለቅሶ ድምጽ ተሰማት፡፡ ያ ደጉ መነኮስ "ጌታ ሆይ! ይቅር በለኝ?" እያለ በተደጋጋሚ ይጮሃል፡፡ ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ "እርሱ በንጽሕና እየኖረ ስለ ነፍሱ እንዲሕ ከተማጸነ እኔማ እንደምን አይገባኝ!" ብላ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡

የለበሰችውን ልብስ ሳትቀይር፣ ቤተሰቦቿን ሳትሰናበት ከቤቷ አተር በዘንቢልና ውሃ በትንሽ እቃ ይዛ ወደ ጐልጐታ ገሰገሰች፡፡ በጌታችን መቃብር ላይም ወድቃ አለቀሰች፤ "ጌታ ሆይ! ነፍሴን ወደ ዕረፍት አድርሳት፣ ከክፉ ጠላትም ጠብቀኝ፣ ይሕንን አተርና ውሃ ለእድሜ ዘመን ሁሉ ባርክልኝ" ብላ ጸለየች፡፡ ፈጥናም ከኢየሩሳሌም ተነስታ ቃዴስንና ሲናይ በርሃን በእግሯ አቁዋርጣ ግብፅ ደረሰች፡፡ ምርጫዋ ብሕትውና ሆኗልና ልምላሜ ከሌለበት ፀሐዩ እንደ ረመጥ ከሚፋጅበት በርሃ ገባች፡፡ በዚያም ከያዘችው አተር ለቁመተ ሥጋ እየበላች፣ ከውሃውም በጥርኝ እየተጐነጨች፣ ከሰው ጋር ሳትተያይ በፍጹም ተጋድሎ ለ38 ዓመታት ቆየች፡፡ የቀኑ ሐሩር: የሌሊቱ ቁር ልብሷን ቆራርጦ ቢጨርሰው እግዚአብሔር ፀጉሯን አሳድጐ አካሏን ሸፈነላት፡፡

ጊዜ ዕረፍቷ ሲደርስ የቅዱሳንን ዜና የሚጽፈው ታላቁ አባ ዳንኤል ወደ እርሷ መጥቶ ሲያያት ተከተላት፡፡ እርሷ ግን በተሰነጠቀ አለት ውስጥ ገብታ ተደበቀች፡፡ አባ ዳንኤልም ሴት መሆኗን አላወቀምና በውጪ ሆኖ "እባክህ አባቴ! ውጣና ባርከኝ" በማለት ተማጸነ፡፡ እርሷ ግን "ራቁቴን ነኝና አልወጣም" አለችው፡፡ መደረቢያውን አውጥቶ ሰጥቷት በፈቃደ እግዚአብሔር ዜናዋን ሁሉ አወቀ፡፡ ወደ በዓቷ ዘወር ሲል በዘንቢል የሞላ አተር ተመለከተ፡፡ ለ38 ዓመታት ተበልቶ ዛሬም ሙሉ ነው፡፡ አባ ዳንኤል ይፈትነው ዘንድ ከአተሩ በደንብ በላለት፡፡ ከውሃውም ጠጣለት ሊጐድል ግን አልቻለም፡፡ እያደነቀ "እናቴ ሆይ! ልብሴን ውሰጂው" ቢላት "ሌላ አዲስ አምጣልኝ" አለችው፡፡

ይዞላት በመጣ ቀን ግን ተሠውራለችና አላገኛትም፡፡ አንድ ቀን ግን አረጋውያን መነኮሳት መጥተው "አንድ ሰው ተመልክተን ወደ በዓቱ ስንገባ አተር በዘንቢልና ውሃ በመንቀል አገኘን፡፡ ስንበላው ወዲያው አለቀ" አሉት፡፡ አባ ዳንኤል ነገሩን ገና ሳይጨርሱለት አለቀሰ፡፡ አተሩ አለቀ ማለት ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ አርፋለች ማለት ነውና፡፡ አረጋውያኑ ግን ቀጠሉ "ከበዓቱ ስንወጣ በጸጉሯ አካሏ ተሸፍኖ ወደ ምሥራቅ ሰግዳ አርፋ አግኝተን ከሥጋዋም ተባርከን ቀበርናት" አሉት፡፡ አባ ዳንኤል ዜናዋን ጽፎላት ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ታከብራታለች፡፡ ገዳማውያን አባቶችና እናቶቻችን ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ትተዋታልና ዓለም የሌላት በረከት በእነርሱ ዘንድ ይገኛል፡፡ በዓታቸውን ስናጸና ገዳማቸውን ስንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡ የቅድስት ዓመተ ክርስቶስ የጸሎቷ በረከት ይደርብን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ድርሹ ዳና የፓርላማ  እጩ ሆነች ጋዜጠኛ እና የማሰታወቅያ ባለሙያ እንዲሁም የሶሻል ሚዲያ ተፅኖ ፈጣሪ የሆነችው ድርሹ ዳና  የፊታችን ወር መጨረሻ ለሁለተኛ  ጊዜ ለሚካሄደው አለም አቀፍ የሴ...
06/04/2025

ድርሹ ዳና የፓርላማ እጩ ሆነች

ጋዜጠኛ እና የማሰታወቅያ ባለሙያ እንዲሁም የሶሻል ሚዲያ ተፅኖ ፈጣሪ የሆነችው ድርሹ ዳና
የፊታችን ወር መጨረሻ ለሁለተኛ ጊዜ ለሚካሄደው አለም አቀፍ የሴቶች ፓርላመንት ላይ እጩ ሆናለች ።
እንደሚታወቀው የ3 ሴት ልጆች እናት ሆና በተሰማራችበት የሚዲያ ሰራ ሰኬት እና ብራንድ አምባሳደር በሆነችበት የኢትዮጵያ አልኮል ፍሪ ጄኔሬሽን ባለው ሰራ እጩ ተደርጋ ተመርጣለች ።
እንኳን ደስ ያለሽ 👏🏽

 50 ሜጋ ፒክስል Autofocus ካሜራ፣ ፈጣን 120 ሀርዝ MTK D7020 6mm 5G ቺፕ፣ 6.78 ያሻዎትን መስራት የሚያስችል ሰፊ ስክሪን፣ 5000 ሚሊ አምፒር ንቅንቅ የማይል ባትሪ ከ...
06/04/2025



50 ሜጋ ፒክስል Autofocus ካሜራ፣ ፈጣን 120 ሀርዝ MTK D7020 6mm 5G ቺፕ፣ 6.78 ያሻዎትን መስራት የሚያስችል ሰፊ ስክሪን፣ 5000 ሚሊ አምፒር ንቅንቅ የማይል ባትሪ ከ 33ዋት የቻርጅ አቅም ጋር ይህ ሁሉ በአንድ ስልክ!! በዚህ ላይ የቴክኖ ካሞን 30 5Gን ሲገዙ የ500 ብር የሞባይል ካርድ ይንበሸበሻሉ፡፡ ይህን ለተወሰነ ጊዜ የሚቆይ ዕድል ሳያመልጦት ይጠቀሙበት!!




ተበዳዩ ካሰን፣ ለሰማያዊው ክብራችን ዋጋ ከፈለልንየ5500 የሰው ልጅ ታሪክ የሚያሳየው ሰው ከገነት እንደ ወጣ አለመመለሱን ነው፡፡ ይህ ታሪክ የተቄረው በክርስቶስ መምጣት ነበር፡፡ በማቴ 1÷...
06/04/2025

ተበዳዩ ካሰን፣ ለሰማያዊው ክብራችን ዋጋ ከፈለልን

የ5500 የሰው ልጅ ታሪክ የሚያሳየው ሰው ከገነት እንደ ወጣ አለመመለሱን ነው፡፡ ይህ ታሪክ የተቄረው በክርስቶስ መምጣት ነበር፡፡ በማቴ 1÷21 እንደተጻፈው ገና ከቅድስት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ሲፀነስ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ ተብሎ ለዮሴፍ ተነገረው፡፡ በዚህ መሠረትም ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኒት ሆኖ መጣ፡፡ በግሪክ ቋንቋ ኢየሱስ ማለት አዳኝ ማለት ነው፡፡ መልአኩ ለዮሴፍ እንደ ነገረው የሚያድነው ደግሞ ያመንነውን እኛን ነው፡፡ ገና ሲፀነስ መድኃኒት መሆኑ የተነገረን መድኃኔ ዓለም /የዓለም መድኃኒት/ ክርስቶስ ልዩ አምላክ ነው፡፡ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር መጥቶ ስለ ኃጢአታችን ተሰቅሎ ሲሞት መንግሥቱን የመውረስ ልጅነት ተሰጠን፡፡ ስንፈጠርም ጀምሮ የእግዚአብሔር ዕቅድ ግን ሰው በመንግሥቱ እንዲኖር ነበር፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ፈጥሮ በገነት ያኖረው አዳም በድሎ ከገነት ወጣ፡፡ በ1ኛ ዮሐ 4÷14 “እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን” ተብሎ እንደተጻፈ፤ አብ ልጁን የዓለም መድኃኒት አድርጎ በመላኩ ታረቀን፡፡ ከገነትም አትብሉ የተባልነውን በልተን በኃጢአታችን ምክንያት ለተባረርነው በቀራንዮ በፈሰሰው ደሙ ከኃጢአታችን ታጥበን መድኃኔ ዓለም ነጻ አወጣን፡፡ አብ አንድያ ልጁን ላከው ስንል ወልድ በመላኩ ከአብ አንሶ አይደለም፡፡ አብና መንፈስ ቅዱስ ከድንግል ማርያም አልተወለዱም፡፡ ከድንግል ማርያም የተወለደው ወልድ ክርስቶስ ነው፡፡ ወልድ ከድንግል ማርያም በመወለዱ ከአብም፣ ከመንፈስ ቅዱስም አያንስም፡፡ ወልድ ከአብ ባሕርይ ከፍጥረተ ዓለም ቀድሞ ስለ ተወለደ ነው ልጅ የተባለው፡፡ ልጅ ቢሆንም ከአባቱ ጋር እኩል ነው፡፡

ከእርሱ ጋር የሚስተካከል የሚወደው አንድያ ልጁን መድኃኒት እንዲሆነን የላከልን አብን እናመሰግነዋለን፡፡ የዓለም መድኃኒትነቱን በማሰብ የተላከ ወልድንም እናመሰግነዋለን፡፡ መንፈስ ቅዱስም ምስጉን ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን ስንጠራው ጌታችን ካልን በኋላ መድኃኒታችን እንለዋለን፡፡ መድኃኒትነቱን እንድንረዳው አእምሮአችንን ያነቃልን ጥበብን የገለጸልንን መንፈስ ቅዱስንም እናመሰግነዋለን፡፡ ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት መሆኑን አይተናል፡፡ መድኃኒት መድኃኒትነቱ መሞከር አለበት፡፡ መድኃኒትን የሰሩ ሰዎች መጨረሻ ደግሞ ለታሰበለት ሰው መድኃኒቱ ተሞክሮ ይታያል፡፡ በሉቃ 24÷42፡43 እንደተጻፈው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎ እያለ የተሰቀለው አንደኛው ወንበዴ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ አለው፡፡

ወንበዴው ያሰቀለው የፈጸመው ግፍ በደል ነው፡፡ ይህን ወንበዴ ሳይቀር ክርስቶስ መድኃኒቱ ሆነና በፈሰሰው ደሙ አጥቦት ዛሬ በገነት ከኔ ጋር ነህ በማለት ወደ መንግሥቱ እንዲገባ አደረገው፡፡ ወንበዴውን ሳይቀር ይቅር ብሎት ወደ መንግሥቱ አስገባው፡፡ እንዲህ ለወንበዴው መድኃኒትነቱን ያሳየን እኛም እንድንጽናናና ወንበዴውን ያዳነ ለእኛም መድኃኒት ነው በማለት ነፍሳችን እንድታርፍ ነው፡፡ እረፍት ላጣችው ነፍሳችን መድኃኔ ዓለም የዘለዓለም እረፍት፣ የክብር ቦታ እንዳዘጋጀላት የነገራት በደሙ ዋጅቶ ነው፡፡ ይህን መዋጀት የተረዱ ገዳማውያን ዓለምን ትተው በምናኔ ይኖራሉ፡፡ በጾምና በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ዮስቴና ከምትባል የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና ሳለች በጾም፣ በጸሎት፣ በምጽዋትና ...
06/03/2025

የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ዮስቴና ከምትባል የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ።

እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና ሳለች በጾም፣ በጸሎት፣ በምጽዋትና በስገድትም የምትጋደል ነበረች። በኋላም ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።

በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕግ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።

አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር።

በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ አምስት መቶ ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፣ የቅዱስ ማቴዎስንና የማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ፣ የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ እንደ ሰጠው ቃል ኪዳን ገባለት።

ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክትም ሁላቸው እየተደሰቱ “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

Address

Washington D.C., DC

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Enawra - ኑና እናውራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share