Enawra - ኑና እናውራ

Enawra - ኑና እናውራ The best online entertainment for Ethiopians
(1)

የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምልጃቸው እና ረድኤታቸው አይለየን 🙏ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ...
09/15/2025

የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምልጃቸው እና ረድኤታቸው አይለየን 🙏

ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ፣ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩ፣ ስለሀገራችን መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው የጸለዩ፣ ከጌታችን ጋር መሞት አይገባኝም ብለው የተከራከሩ ታላቅ ጻድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡

ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር ሲቆዩ በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ ይህም ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን እየለመኑ ነው፡፡ በተጋቡ በሰላሳ ዘመናቸው አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ክብሩና ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል ክህነቱ እንደ መልከጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡

መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ ያማረ ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ በተወለደበት ቅጽበት አንደበቱ ሲያመሰግን የተገኘ፣ ወንድ ልጅ ወለደች። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ባረከችው ቅዱሳን መላዕክት ዘወትር ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡
ሕፃኑንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ሰጡት፡፡

ፍጹም የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮበታልና ሥራው ሁሉ በዕውቀት የተመላና የተቃና ሆነ፡፡ እንደ ቅዱስ እንጦንስም አስኬማ ሰጥተው አመንኮሱት፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ ወደ ሰማያት አርገው በረከትና ጸጋ የተቀበሉ፣ አጋንንትን የሚያሳድዱበት፣ ታላቅ ጸጋ ተሰጣቸው፡፡ ሰውነታቸው አንድ ክንድ ከስንዝር በሚረዝም ጠጉር የተሸፈነው አባታችን ወደ ሀገራችን መጥተው ተጋድሏቸውን ቀጠሉ፡፡

ከሰው ተለይተው ወደ ዱር ገብተው ከስድሳ አንበሶችና ከስድሳ ነብሮች ጋር የሚኖሩት አባታችን፣ እንስሳቱ እርሳቸውን የረገጡትን መሬት ልሰው ጠግበው ይኖራሉ። የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ገዳማቶቻቸው ወዳሉባቸው ወደ ምድረ ከብድና ወደ ዝቋላ ተራራ ወሰዳቸው፡፡ በእነዚህ ገዳማት እየተመላለሱ ሲጸልዩና ሀገራችንን ሲባርኩም ኖረዋል፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ በሀገራች ያለውን የኃጢአት ስራ ባዩ ጊዜ በዝቋላ ሐይቅ አንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው መላው ኢትዮጵያን እንዲምርካቸው ጸልየው ቃል ኪዳን ተቀብለዋል፡፡ በመጨረሻም መጋቢት 5 በምድረ ከብድ አቦ ገዳም አርፈው ጌታችን በመላእክት ምስጋናና ዝማሬ ነድሳቸውን በታለቅ ክብር ተቀብሏታል። ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ዓለምን ንቀው ለጌታችን ተገዝተዋል፤ ገዳማቱን እንርዳ በዓታችውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

በኀጢአታችን ተስማምቶ ሳይሆን የንስሐ ጊዜ ሲሰጠን ነው ሀገሩ በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከተማ ከ“ዓናቶት” ነው፤ ትውልዱም ከካህናት ወገን እንደነበረ በትንቢቱ መግቢያ ተጽፏል፡፡ ከአራቱ ዓ...
09/14/2025

በኀጢአታችን ተስማምቶ ሳይሆን የንስሐ ጊዜ ሲሰጠን ነው

ሀገሩ በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከተማ ከ“ዓናቶት” ነው፤ ትውልዱም ከካህናት ወገን እንደነበረ በትንቢቱ መግቢያ ተጽፏል፡፡ ከአራቱ ዓበይት ነቢያት አንዱ ሲኾን የቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ትውፊት አባቱ “ኬልቅያስ” እናቱ ደግሞ “ማርታ” ይባላሉ፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ እንደ ነቢዩ ሳሙኤል፤ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ለነቢይነት የተለየው ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ነው፡፡ “ኤርምያስ” ማለት “እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያደርጋል” ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ ለእስራኤል ብቻ ሳይኾን ለአሕዛብም ጭምር ነቢይ እንዲሆን በተጠራ ጊዜ ደንግጧል፤ “ሕፃን አንድም ሕፃነ አእምሮ ነኝና ወዮልኝ” በማለትም አመንትቷል፡፡ በኋላ ግን እግዚአብሔር፡- “እስራኤልና አሕዛብን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፣ ከገቢረ ኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ ትመልሳቸዋለህና ሕፃን ነኝ” አትበል ተብሎ በተሰጠው ተስፋ መሠረት በረታ፡፡

አገልግሎቱን የጀመረው ከ640-609 ዓ.ዓ በነገሰው በይሁዳው ንጉሥ ኢዮስያስ በ13ኛው ዓመት በ626 ዓ.ዓ ላይ ነበር፡፡ ይሕ ዓመት እጅግ በጣም ወሳኝ ነበር፡፡ በአንድ በኵል ንጉሥ ኢዮስያስ ባዕድ አምልኮን ለማስወገድ፣ የእግዚአብሔርን ቤትና አምልኮ ለማሳደስ ከጀመረ አንድ ዓመት ኾኖታል፡፡ በሌላ በኵል ደግሞ ባቢሎናውያን ከአሦር አገዛዝ ነፃ ለመውጣት አንድ ዓመት ይቀራቸው ነበር፡፡ ስለዚኽ ነቢዩ ኤርምያስ አገልግሎቱን የጀመረው በቤተ ክህነቱም በፖለቲካውም ወሳኝ ኩነቶች የሚፈጸሙበት ሰዓት ላይ ነበር ማለት ነው፡፡ የሕዝቡን ግብረ ገብነት ስንመለከት በቤተ መቅደስ ሔደው መሥዋዕት ስላቀረቡ ብቻ እግዚአብሔርን ከልባቸው ያመለኩት ይመስላቸው ነበር፡፡ በዘኑ በይሁዳ ነግሠው የነበሩት ነገሥታት አምስት ቢሆኑም ከኢዮስያ ዘመን ጀምሮ ለ23 ዓመታት አስተምሯል፡፡

ከሌሎች ነቢያት ይልቅ እጅግ ጸሎተኛ እንደሆነ የሚነገርለት ኤርምያስም ሕይወታቸው ወደ ኾነው እግዚአብሔር እንዲመለሱ ያለማቋረጥ ለ23 ዓመታት ይጠራቸው ነበር፡፡ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በይሁዳ ላይ ብቻ ሳይኾን በብዙ ሕዝቦች ላይ እንደሚመጣ፣ እስከ 70 ዓመትም ድረስ እነዚህ ሕዝቦች ለባቢሎን እንደሚገዙ ተነበየ፡፡ ህዝቡንም እግዚአብሔር ግን ከመሥዋዕት ይልቅ ልብን ይፈልጋልና ከልባቸው ካልተመለሱ በባዕድ ንጉሥ እንደሚማረኩ ቤተ መቅደሱም እንደሚፈርስ በቤተ መቅደሱ በር ሆኖ በመጮህ በግልጽ ነገራቸው፡፡ ሕዝቡና ካህናቱ ግን አላመኑትም፡፡ ይባስ ብለዉም በኤርምያስ 20÷2 እንደተጻፈው፤ ብዙ መከራ አደረሱበት፡፡ አምስቱ መጻሕፍቱም ትንቢተ ኤርምያስ፣ ተረፈ ኤርምያስ፣ ሰቆቃወ ኤርምያስ፣ መጽሐፈ ባሮክ፣ ተረፈ ባሮክ ናቸው፡፡

የትንቢቱ ዋና መልዕክት እግዚአብሔር ታላቅና ቅዱስ ስለሆነ ሕዝቡ ከክፋት ተመልሰው በፍጹም ልብ እንጂ በሐሰት እንዳያመልኩት ማስገንዘብ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ! እኛስ? እኛስ መፃተኛውን አልበደልንምን? ድኻ አደጉን አላንከራተትንምን? መበለቲቱን አላስከፋታንምን? እድንመለስ ስንት ጊዜ ተናገረን? ታድያ ቤተ መቅደሱ ሰውነታችን እስኪፈርስ ድረስ እየጠበቅን ነው? እግዚአብሔር እስከ ዛሬ ድረስ የጠበቀን ከኀጢአታችን ጋር ተስማምቶ ሳይሆን የንስሐ ጊዜ ሲሰጠን ነው፡፡ ዓለምን የናቁ፣ ለጽድቅ ስራ የነቁ ገዳማውያን ሌሊትና ቀን በጾምና በጸሎት የመትጋታቸው ምስጢር ከልባቸው መመለሳቸው ነው፡፡ አብነት እናድርጋቸው፣ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ፣ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

እንደ ነቢዩ ኤልያስ ለጓሜ ደመና የተባሉ  እንደ ሊቀ ነቢያት ሙሴ የተለያዩ ጠበሎችን ከዐለት እያፈለቁ ድዉያንን የፈወሱ፤ ቅዱስ ላሊበላም ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶቹ ውስጥ አንደ...
09/13/2025

እንደ ነቢዩ ኤልያስ ለጓሜ ደመና የተባሉ

እንደ ሊቀ ነቢያት ሙሴ የተለያዩ ጠበሎችን ከዐለት እያፈለቁ ድዉያንን የፈወሱ፤ ቅዱስ ላሊበላም ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶቹ ውስጥ አንደኛውን "ቤተ አባ ሊባኖስ" ብሎ በስማቸው የሰየመላቸው፣ በጸሎታቸው ኀይል ለሦስት ዓመት ሰማይን የለጎሙና እንደ ቴስቢያዊው ነቢዩ ኤልያስ ለጓሜ ደመና የተባሉ፣ ታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ገዳም በስማቸው የተጠራላቸው፣ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትንም መስርተዋል፡፡ አሁን ገዳሟ ያለችበት ስፍራ በ485 ዓ.ም የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔ ዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠው ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ ሔደዋል። ከ16 ዓመታት በኋላ በ500 ዓ.ም ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው፣ ጠበሏን አፍልቀው፣ ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡

በ1967 ዓ.ም አንድ ምእመን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን አስፈቅደው፤ ከአኵሱም ገድላቸውን አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ ገንዘብ እየከፈሉ ጻድቁን አዘክረዋል፡፡ ከጥር 3 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮም በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም የጻድቁ ክብረ በዓል በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል። ተአምረኛው አባት አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ የከበረ ዐፅማቸው ያረፈበት ገዳም ደብረ ወርቅ ሐም የሚገኘው በኤርትራ ነው፡፡ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልም “ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ክብርህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናለህ” ብሎ ነው እየመራ ያመጣችው፡፡

እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን የወንጌልን ብርሃን ያበሩ ታላቅ ሐዋርያ፣ እጅግ የከበሩና ድንቅ ተአምራትም የሰሩ ጻድቅ ናቸው። በአንድ ወቅት ሰዎች በሰሜን ካለ ሀገር አንድ በጽኑ የታመመ ሰው በአህያ ጭነው አመጡና "ስለ እግዚአብሔር ብላችሁ ወደ አባታችን አባ ሊባኖስ ቦታ ውሰዱን" አሏቸው። የቦታውም ሰዎች ባዩት ጊዜ መልኩ እጅግ ተለውጦና ልብሱም ከሰውነቱ ጋር ተጣብቆ ነበርና ናቁት እንጂ አልተቀበሉትም። ስለዚህም ያመጡትን ሰዎች መልሰው እንዲወስዱት ግድ አሏቸው፣ ከመሬት አንሥተውም በአህያ ጭነውም ወዳመጡበት መልሱት፡፡ ያም ሕመምተኛ በተደረገበት ነገር እጅግ አዘነ፣ ወደ ጻድቁም ጸለየ፡፡

"ክቡር አባቴ አባ ሊባኖስ ሆይ እኔ እንደ አንተ ክርስቲያናዊ እሆናለሁ፣ እድናለሁ ብዬ ብመጣ ከዚህ ከቤትህ ያሉ ሰዎች ጠሉኝ፣ የእግዚአብሔር ቅዱስ አባ ሊባኖስ ሆይ! መገፋቴን ተመልከት..." እያለ አሰምቶ እየጮኸ አለቀሰ፡፡ የተሸከሙት ደጋግ ሰዎችም ስሟ አጥቃዕሎ በምትባል ከአባታችን ቦታ ሁለት ምዕራፍ በምታስኬድ ስፍራ በደጃፉ ላይ እንደ ድንጋይ አስቀመጡትና ብቻቸውን ትተውት ሔዱ። አባታችን አቡነ ሊባኖስም በታላቅ ግርማ ሲመጡ ሕመምተኛውም ባያቸው ጊዜ ፈራ። በእጃቸውም እግሩንና ደረቱን ይዘው ልብሱ እስከሚበጣጠስ ድረስ አቃኑት። ይኽንንም ታላቅ ተአምር የሰሙ ሁሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፣ ገባሬ ተአምር አባታችንንም አመሰግኗቸው። ቃልኪዳናቸውም ከደዌ ስጋና ከደዌ ነፍስ ሕሙማንን ይፈውሳል፡፡ ገዳማውያን ዓለምን ስለጌታችን ፍቅር ትተዋልና ክብራቸው ከፍ ያለ ነው፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

በአዲሱ አመት በአዲስ ምዕራፍ፣ በአዲስ አልበም ከጆኒ ራጋ ጋር በአዲሱ ቴክኖ ካሞን 40! መልካም አዲስ አመት!
09/12/2025

በአዲሱ አመት በአዲስ ምዕራፍ፣ በአዲስ አልበም ከጆኒ ራጋ ጋር በአዲሱ ቴክኖ ካሞን 40! መልካም አዲስ አመት!

ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣምሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልና አባቱ ካህኑ ቅዱስ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን ያገለገለ፤ በፍጹም ልቡ ዓለምን የናቀ፤ ...
09/12/2025

ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልና አባቱ ካህኑ ቅዱስ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን ያገለገለ፤ በፍጹም ልቡ ዓለምን የናቀ፤ ከተድላዋና ከደስታዋም የተለየ፤ አምላክን ለማጥመቅ የታደለ ሐዋርያ፣ መምህር፣ ሰማዕት፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ ነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፡፡ ሊቁም ከመላእክት፣ ከነቢያት፣ ከካህናት፣ ከሐዋርያት መካከል እንደርሱ መለኮትን ለማጥመቅ የተመረጠ አለመኖሩን በመጥቀስ “ዮሐንስ ሆይ! ራጉኤል በትጋቱ፣ ኢዮብም በጽድቁ ቢመኙም ሆነ ቢጨነቁ እንደ አንተ የሚነድ እሳት መለኮትን ሊያጠምቁ አልተቻላቸውም” ሲል ታላቅነቱን መስክሮለታል፡፡ ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ በሉቃስ 1÷14 እደተጻፈው ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና ዮሐንስ ማለት ተድላና ደስታ ማለት ነው፡፡ ካህኑ ዘካርያስና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ በሕገ እግዚአብሔር የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ፡፡

ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን ዘወትር ይማጸኑት ነበር፡፡ ካህኑ ዘካርያስ በቤተ መቅደስ ዕጣን ሲያሳርግ ቅዱስ ገብርኤል በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ጸሎቱ እንደ ተሰማና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ እንደምትወልድ፤ ስሙንም ዮሐንስ እንደሚለው፤ በመወለዱም ብዙዎች እንደሚደሰቱ፤ ልጁም በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ እንደሚኾን፤ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ እንደማይጠጣ፤ እንደዚሁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላበት ነገረው፡፡ ካህኑ ዘካርያስም “እኔ ሽማግሌ ነኝ፤ ሚስቴም አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ?” አለው፡፡ መልአኩም “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፡፡ እነሆም በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ ይህ ነገር እስከሚኾን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ፤ መናገርም አትችልም” አለው፡፡

እርሱም ድዳ ሆኖ ኖረ፡፡ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሔደ፤ ከሁለት ቀን በኋላም አረጋዊቷ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፀነሰች፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም በመካንነቷ ከሰዎች የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዷላታልና “እግዚአብሔር በዚህ ወራት ከሰው ስድቤን ያርቅ ዘንድ እንዲህ አደረገልኝ” ስትል ለአምስት ወራት ተሸሸገች፡፡ የመውለጃዋ ቀን ሲደርስም ዘመነ ብሉይ ሊፈጸም፣ እግዚአብሔር በሥጋ ሊገለጥ ስድስት ወራት ሲቀረው፣ ሰኔ 30 ቀን ንዑድ፣ ክቡር የኾነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ፡፡ ዘመዶቹ ስሙን በአባቱ መጠርያ ዘካርያስ ሊሉት ቢወዱም እናቱ ግን ዮሐንስ ይባል አለች፡፡ የመልአኩን የብሥራት ቃል ባለመቀበሉ አንደበቱ ተይዞ የነበረው ካህኑ ዘካርያም ስሙ ዮሐንስ› ይባል ብሎ ሲጽፍ አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱም ተፈታ፡፡

በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም “አንተ ሕፃን ሆይ! የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና፡፡” ሲል አመሰገነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በማቴዎስ 11÷7-11 “ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጥታችኋል? ከነፋስ የተነሣ የሚወዛወዛውን ሸንበቆ ነው? ወይስ ምን ልታዩ መጥታችኋል ቀጭን ልብስ የለበሰ ሰውን ነውን? እነሆ ቀጭን ልብስ የሚለብሱማ በነገሥታት ቤት አሉ? ምን ልታዩ መጥታችኋል ነቢይ ነውን? አዎን እርሱ ከነቢያት እጅግ ይበልጣል፤ እነሆ በፊትህ መንገድህን የሚጠርግ መልእክተኛዬን እልካለሁ ተብሎ ስለ እርሱ የተጻፈለት ይህ ነውና፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ ሴቶች ከወለዷቸው ወገን ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም” ሲል መስክሮለታል፡፡ መስከረም 2 ቀን በሰማዕትነት ያረፈበት ቀን ነው፡፡ ገዳማውያንም የዓለም አምሮታቸውን ገድለው የነፍሳቸውን ድህነት ሲከተሉ አብነት ያደርጉታል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጽና የበረከታቸው ተሳታፊ እሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

‎ልበ ቅን የሆኑ ሁለቱ ባለጸጋዎች የአዲስ አመት በዓልን ከምስኪናን ጋር አሳለፉ‎‎የባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት የምንጊዜም  አጋርና አምባሳደር  ወጣቱ ባለጸጋ ምረትአብ ሙሉጌታ  እና ...
09/11/2025

‎ልበ ቅን የሆኑ ሁለቱ ባለጸጋዎች የአዲስ አመት በዓልን ከምስኪናን ጋር አሳለፉ

‎የባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት የምንጊዜም አጋርና አምባሳደር ወጣቱ ባለጸጋ ምረትአብ ሙሉጌታ እና የአፍሮ ሊንክ ግሩፕ ባለቤት አቶ ሚኪያስ አያሌው በዛሬው ዕለት መስከረም 1/2018 ዓ/ም የዘመን መለወጫ በዓልን ባቡል ኸይር ድርጅት ምሳ በማብላት እና ድጋፍ በማድረግ በአልን ከምስኪን ወገኖቻችን ጋር አሳለፉ።

‎አቶ ሚኪያስ አያሌው 5 ሺ ለሚሆኑ ወገኖች ሙሉ የምሳ ወጪ በመሸፈን ምሳ ያበላ ሲሆን ምረትአብ ሙልጌታ ደግሞ የ500 ሺ ብር ድጋፍ አድርጓል።

‎ሁለቱ ባለጸጋዎች በዓልን ከምስኪናን ጋር ማሳለፋችን እጅግ ደስታ ሰጥቶናል እኛ ኢትዮጵያዊያኖች እርስ በእርሳችን መረዳዳትና መደጋገፍ አለብን ባቡልኸይር እየሰራው ያለው በጎ ተግባር እጅግ የሚያሥደስትና የሚያኮራ ስለሆነ ሁላችንም በትርፍ ጊዜያችን በባቡልኸይር እየተገኘን ከምስኪን ወገኖቻችን ጋር እያሳለፍን ተዝቆ የማያልቀውን የእናቶችን እና የአባቶችን ምረቃ ተቀብለን ልንባረክ ይገባል ብለዋል።

‎የባቡልኸይር በጎ አድራጎት መስራች ከሆኑት መካከል አንዷ የሆነችው ወይዘሮ ፈትያ መሐመድ
‎የምንጊዜም ደጋፊያችን ሚኪና ምረትአብ በዛሬው ዕለት በአልን ከቤተሰቦቻችሁ ጋር ማሳለፍ እየቻላችሁ አስታዋሽ የሌላቸው እናቶቻችን እና አባቶቻችን ይበልጡብናል ብላችሁ ምሳ አብልታችሁ የ 500 ሺ ብር ድጋፍ አድርጋችሁ አብራችሁን ስለዋላችሁ ፈጣሪ በወጣ ይተካላችሁ በረካ ሁኑልን እጅግ አድርገን እናመሠግናችኋለን በማለት ምስጋናዋን ገልጻለች።

እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏 #ዕንቍ ዕጣ ወጣሽልኝየጥበብ ቤት፣ በክርስቶስ ደም የተመሰረተች፣ በሐዋርያት ትምህርት የጸናችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ምጡቅ የሆነ...
09/11/2025

እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏

#ዕንቍ ዕጣ ወጣሽልኝ

የጥበብ ቤት፣ በክርስቶስ ደም የተመሰረተች፣ በሐዋርያት ትምህርት የጸናችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ምጡቅ የሆነውን የዘመን ቀመር ፈጥራ ለዓለም አስረክባለች፡፡ የኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት በዓለማችን ልዩና ጥንታዊ ከሚባሉት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ መስከረም 1 የአዲስ ዘመን ብስራት የብሩህ ተስፋ መጀመሪያ ነው፡፡ እለቱ እንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ፣ ርዕሰ ዐውደ ዓመት ተብሎ ይጠራል፡፡ እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜ መነሻው ኖኅና ልጆቹ ከጥፋት ውሃ በኋላ ሰማዩ በደመና በመክበዱ የጥፋት ውሃ እንደገና ይዘንም ይሆን እያሉ ሲደነግጡ ከርመው በመስከረም ወር መጀመሪያ ላይ ሙሉ የፀሓይ ብርሃን ስላዩ፣ ምድር በአበባ አሸብርቃ ስለ ተገለጠችና በዚህም የእግዚአብሔርን ቸርነት የቃል ኪዳኑን መጽናት ስለ ተረዱ ይህንን በዓል ቀድሞ ከአባቶቻቸው እንደ ወረሱት ያው ጥንተ ብርሃን ጥንተ ዓመት ጥንተ ዕለት አድርገው አክብረውታል።

ሲያከብሩትም እንግጫ ነቅለው፣ አበባ ጐንጕነው መጀመሪያ መሥዋዕት ይሠውበት ከነበረው ቦታ ሄደው ለእግዚአብሔር ገጸ በረከት ካቀረቡ በኋላ እርስ በርስም የአበባ ስጦታ በመለዋወጥ ነበር። ሲያከብሩትም ዕንቍጣጣሽ በሚል ቃል እውነተኛ መልካም ምኞታቸውን ይገላለጡበት ነበር። በሌላ በኩል ዕንቍጣጣሽ ማለት ተንቈጠቈጠ፣ አንቈጠቈጠ ከሚለው ቃል የተወሰደ ምድር በአበባ አጌጠች፣ ሰማይም በከዋክብት አሸበረቀ፣ ሰማይን በከዋክብት ያስጌጠ አምላክ ምድርንም በአበቦች አጎናጸፋት ለማለት የተሰጠ ቃል ነው፡፡ ሁለተኛም ጥንታዊያን አባቶቻችን ኢትዮጵያን በሙሉ ሀብት ተረክበዋት ነበርና “ዕንቍ ዕጣ ወጣሽልኝ” ሲሉ ወደ አገራቸው ሲገቡ ለአገራቸው መታሰቢያ አድርገው የተጠቀሙበት ቃል ነው ይባላል።

በመሠረቱ ግን ያ የጥፋት ውሃ ቆሞ ምድር ጸንታ፣ አበባ ቋጥራ፣ ፍሬ ለመስጠት ተዘጋጅታ መገኘቷን የሚያበሥር ቃል ነው። በግእዝ ቋንቋ መርከብ መስቀር ይባላል። የኖኅ መርከብ እንደ ዕብራውያን አቈጣጠር ሰባተኛ በሆነው በመስከረም ወር መጀመሪያ ላይ በአራራት ተራራ አናት ላይ ዐርፋለች። ከዘመን ብዛት በኋላ «ቀ» ወደ «ከ» ተለውጦ መስከረም ተባለ እንጂ መስቀርም ምድር አገኘች፣ ወይም መርከቧ ምድር ነካች ለማለት የተሰጠ የወሩ ስያሜ ነው። ዐውደ ዓመት መባሉም፣ ዐውድ ማለት በግእዙ ቋንቋ ዙሪያ፥ ክብ የሆነ ነገር ማለት ነው። የዓመት ጠቅላላ ቀኖች መሠረታውያን ቀኖች የሚባሉት ሦስት መቶ ስድሳ አራት ቀኖች ናቸው። እነዚህም በኀምሳ ሁለት ሱባዔ ተከፍለው ለእያንዳንዱ ቀን በዓመት ውስጥ ለሰባቱ ዕለታት ኀምሳ ሁለት ኀምሳ ሁለት ቀን ይደርሳቸዋል።

ከነዚህ ቀኖች የተሳሳበ የሴኮንድ፣ የደቂቃ፣ የሰዓት ዕላፊ ተጠራቅሞ 365ኛዋን የዘመን ማገጣጠሚያ ቀን ያስገኛል። ስለዚህም ዕለቲቱ ዙሪያ፣ ክብ መግጠሚያ ወደ ዐዲሱ ዘመን መጀመሪያ የምንተላለፍባት ናት ማለት ነው። ዕለት አዕዋዲት፣ ዕለተ ምርያ የመዘዋወሪያ ቀን ወይም የመጨረሻ ቀን ተብላ ትጠራለች። በአራት ዓመት ደግሞ ከዚህች መሳሳብ የምትገኝ አንዲት ቀን ትመጣለች። ሦስት መቶ ስድሳ ስድስተኛ። ይህቺ ቀን ዕለተ ሰግር ትባላለች። መረማመጃ ማለት ነው። አንድ ቀን ታስተላልፋለችና። እንግዲህ እነዚህን ሁለቱን ቀኖች ተከትሎ የሚመጣው ቀን የዘመን መጀመሪያ፥ የዘመን ክብ መነሻና መድረሻ ተብሎ ርእሰ ዐውደ ዓመት ተብሎ በግእዙ ይጠራል። እነዚህ ቀኖች በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር ተጠቃለው አንድ ጊዜ የሚገኙ ናቸው።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ወጣቱ ባለፀጋ ምህረተአብ ሙሉጌታ በአዲስ አበባ ‎ከረዩ ሰፈር ለሚገኙ ለ500 ወገኖች ድጋፍ አደረገ።‎‎ሁሌም በጎ በማድረግ የሚታወቀው ምህረተአብ ሙሉጌታ አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ በዛ...
09/10/2025

ወጣቱ ባለፀጋ ምህረተአብ ሙሉጌታ በአዲስ አበባ ‎ከረዩ ሰፈር ለሚገኙ ለ500 ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

‎ሁሌም በጎ በማድረግ የሚታወቀው ምህረተአብ ሙሉጌታ አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ በዛሬው ዕለት ጳጉሜ 5, 2017 ዓ/ም በልደታ ክፍለ ከተማ ከረዩ ሰፈር ለሚገኙ 500 ለሚደርሱ ወገኖች ለእያንዳንዳቸው 25 ኪሎ ዱቄት እና 5 ሊትር ዘይት ድጋፍ አደረገ።

‎በዝግጅቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

‎ወጣቱ ባለጸጋ ምህረተአብ ባስተላለፈው መልእክት "ሁላችን ብንተባበር ካለን ላይ ብናካፍል ብዙ የሚቸግረው ሰው አይኖርም። ሁሉም ሰው አካባቢው ያለ የተቸገረን ሰው በመለየት ቢያግዝ መልካም ነው" ሲል መልእክት አስተላልፏል።

‎ባለሀብቱ ከህዳሴው ግድብ ምርቃት ጋር ተያይዞ በዝግጅቱ ላይ ደስታውን የገለጸ ሲሆን "ሀገራችን ኢትዮጵያ ከአለም ሀገራት ቀዳሚዋ ትሆናለች በድህነት የሚያውቋት ኢትዮጵያ ከፍ ትላለች" በማለት ተናግሯል።

‎የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ባለሀብቱ ለከረዩ ሰፈር ነዋሪዎች ላደረጉት እገዛ አመስግነው ለመላው የከተማዋ ነዋሪዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።


‎ድጋፉ የተደረገላቸው ነዋሪዎችም በተደረገላቸው እገዛ መደሰታቸውን ገልፀው ወጣቱ ባለሀብት ምህረተአብ ሙሉጌታንና የተባበሩ አካላትን በሙሉ አመሥግነዋል።

ታላቁ ገዳማዊ ሰው በመባል የሚታወቁ ቅዱስ አባት ናቸው፡፡ ከኋለኛው ዘመን ጻድቃን አንዱ ሲሆን ተወልዶ ያደገውም በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በግብጽ ካይሮ ውስጥ ነው ታላቁ ቅዱስ በርሶማ፡፡ ወ...
09/10/2025

ታላቁ ገዳማዊ ሰው በመባል የሚታወቁ ቅዱስ አባት ናቸው፡፡

ከኋለኛው ዘመን ጻድቃን አንዱ ሲሆን ተወልዶ ያደገውም በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በግብጽ ካይሮ ውስጥ ነው ታላቁ ቅዱስ በርሶማ፡፡ ወላጆቹ ክርስቲያኖች ስለነበሩ በሃይማኖትና በምግባር እየኮተኮቱ ቅዱሳት መጻሕፍትንም እያስተማሩ ቢያሳድጉትም በወጣትነቱ አንድ ሰሞን ተከታትለው ዐረፉ:: በወቅቱም ስለ ሃብት ክፍፍል ዘመዶቹ ተናገሩት፡፡ ነገር ግን አንድ ጉልበተኛ አጐት ነበረውና ንብረቱን ሁሉ ቀማው፡፡ ቅዱስ በርሶማ በልቡ “እንዴት ነገ ለሚጠፋ ገንዘብ ፍርድ ቤት እሔዳለሁ?” በማለት ይህችን ዓለም ይተዋት ዘንድ ወሰነ፡፡ ከቤቱም እየዘመረ ወደ በረሃ ገሰገሰ፡፡ በማቴዎስ 16÷26 “ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ካጐደለ ምን ይረባዋል” ተብሎ እንደተጻፈ ነፍሱን ለማዳን ልብሱን በመንገድ ለነዳያን ሰጥቶ ራቁቱን በአምስት ኮረብታዎች ውስጥ ተቀመጠ፡፡

በዚያም የቀኑ ሐሩር፣ የሌሊቱ ቁር፣ ሲፈራረቅበት ለብዙ ዓመታት ኖረ፡፡ እርሱ ግን ያ ሁሉ መከራ እያለፈበት ደስተኛ ነበር፡፡ ዘወትር የዳዊትን መዝሙር ያለ ማቋረጥ ይዘምራል፡፡ የቅዱሳን ገድል እያነበበ መንፈሳዊ ቅናትን ይቀናል፡፡ ያነበባትንም ነገር በተግባር ይፈጽማል፡፡ ይህ ቅዱስ ስለ ራቁትነቱ እንዳይከፋው ዘወትር ራሱን “በርሶማ ሆይ! ከእውነተኛው ዳኛ ፊት ራቁትህን መቆምህ አይቀርምና የዛሬውን ጊዜያዊ ራቁትነትህን ታገስ” እያለ ይገስጽ ነበር፡፡ አንዴ ለጸሎት ከቆመ የሚቀመጠው ከቀናት በኋላ ነው፡፡ ከዕለተ ሰንበት ውጪ ምግብ አይቀምስም፡፡ በእንዲህ ያለ ተጋድሎ እያለ ውዳሴ ከንቱ ስለ በዛበት ሸሽቶ ወደ ምሥር ወይም ግብጽ ሔዶ በቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አደረ፡፡

በዚያም ለሠላሳ ዓመታት ተጋደለ፡፡ በቦታው የጉድጓድ ውኃ ነበርና ሁሌ ሌሊት ወደ ውስጥ ሰጥሞ ይጸልይ ነበር፡፡ እንደ ስለት የሚቆራርጠውን ውርጭም ይታገሥ ነበር፡፡ በዚያ አካባቢ ብዙ ሰውና እንስሳትን የፈጀ አንድ ዘንዶ ስለነበር በአካባቢው ሰው አያልፍም ነበር፡፡ ታላቁ በርሶማ ግን ወደ ዘንዶው ዋሻ ሔደና በማርቆስ 16÷18 እንደተጻፈ “ጌታ ሆይ! በስምህ ለሚያምኑ የሰጠሃቸውን ሥልጣን አትንሳኝ?” ብሎ ጸለየ፡፡ “በአንበሳና በዘንዶ ላይ ትጫናለህ፡፡” የሚለውን መዝሙር ዘመረና ዘንዶውን “ና ውጣ” ብሎ ሲያዝዘው ወዲያው ወጥቶ ሰገደለት፡፡ አገልጋዩም ሆነ፡፡ የአካባቢው ሰዎችም እጅግ ደስ አላቸው፡፡ ብዙ ጊዜም አገልግሏቸዋል፡፡

ታላቁ አባ በርሶማ የሚያርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ ደቀ መዝሙሩን “እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ “የብርቱ የእግዚአብሔር ልጅ” ብሎ ለሚጠራኝ በረድኤት እመጣለታለሁ፡፡” ብሎ ምላሱን በምላጭ ቆርጦ ጣለውና አሰምቶ ዘመረ፡፡ እግዚአብሔር ያበራልኛል፣ ያድነኛልም፡፡ ምን ያስፈራኛል” እያለም ዘመረ፡፡ የሰው ልጅ ምላስ ከሌለው መዘመርም፣ መናገርም አይችልም፡፡ ቅዱሳን ግን ሲበቁ ልሳን መንፈሳዊ ይሰጣቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በትእምርተ መስቀል አማትቦ በ1340 ዓ/ም ዐረፈ፡፡ ፓትርያርኩን አባ ዮሐንስን ጨምሮ ሊቃነ ጳጳሳትና የግብጽ ሹማምንት ገንዘውት ከበረከቱ ተካፈሉ፡፡ ገድሉ እንዳስቀመጠው በዘመኑ ሁሉ ምንጣፍ ላይ ተኝቶ፣ በገዳማዊ ሕይወቱ ሁሉ ልብስ ለብሶ አያውቅም፡፡ “ማዕከለ ሥጋሁ ወምድር ኢገብረ መንጸፈ” እንዲል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

እንኳን አደረሳችሁ ለመላዉ ኢትዮጲያዊያን በሀገር ዉስጥም በዉጭ ሀገር ለምትገኙ ኢትዮጲያዊያን በሙሉ በዓሉ የሠላም የጤና ይሁንላችሁ።አብርሃም ግዛዉ ኢንተርቴመንት ከኦያያ መልቲ ሚዲያ ጋር በመ...
09/10/2025

እንኳን አደረሳችሁ ለመላዉ ኢትዮጲያዊያን በሀገር ዉስጥም በዉጭ ሀገር ለምትገኙ ኢትዮጲያዊያን በሙሉ በዓሉ የሠላም የጤና ይሁንላችሁ።አብርሃም ግዛዉ ኢንተርቴመንት ከኦያያ መልቲ ሚዲያ ጋር በመተባበር "የጥበብ ብልጭታ" የመዝናኛና የመረጃ ኘሮግራም እንኳን ለአዲስ አመት አደረሳቹህ እያለ "

"ዘመንን ከእኛ ጋር" የተሰኘ ልዮ የበዓል ኘሮግራም ይዞላች ይቀርባል። በዓሉ የሰላም የጤና እንዲሆን ይመኛል። ልዮ- ልዮ አዝናኝ የበዓል ኘሮግራሞች በተወዳጅ በብስራት ኤፍ .ኤፍ 101.1 ሐሙስ መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00-6:00 ሰዓት ላይ ይዞላችሁ ይቀርባል::

አዝናኝና አሰተማሪ ድራማ :ጭዉዉቶች ሽልማት የሚያስገኙ ጥያቄና መልስ ዉድድሮች:ከታዋቂ አርቲስቶችና ጋር ቆይታ አዲስ ዓመትን የተመለከተ የኘሮግራሙ አካል ናቸዉ::

በእለቱ የተለያዮ ስጦታዎች በዝግጅቱ እንሰጣለን ከአድማጮች ጋር በቀጥታ ስልክ መስመር እንኳን አደረሳችሁ መልክቶችን ለወዳጅ ዘመድ ያስተላልፍ ያድምጡ ይሳተፍ 0930470847 ወይም 0912374014 የስልክ መስመር እናደርጋለን ያድምጡን ይሳተፍ በአብሊኬሽን ወይም በድረገፅ /www.bisrattv.com/http://www.bisrattv.com http://xn--www-kbpygv3a3m.bisrattv.com/ ወይም www.bisrat fm.com ላይ እና በመላዉ አለም እንደመጣለን።መልካም በዓል www.bisrattv.com
ቀጥታ ስርጭት የሚለውን ይጫኑ
በበዓሉ እለት በለዕለተ ሐሙስ መስከረም 1ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 እስከ 6:00ሰዓት በተወዳጁ ጣብያ ብስራት ኤፍ. ኤም101.1 ላይ።

መልካም በዓል!!!መልካም በዓል!!! ኘሮግራም ስፖንሰሮችንና ስጦታ የሰጡን ተቋማትና ግለሰቦችን እናመሠግናለን።
እጅግ አድርገን እናመሠግናለን በወጣ ይተካ ክብረት ይስጥልን።

በመንግስተ ሰማያት እንድታይን በዚህ ይቅርብሽይህ ቅዱስ አባት የ4ኛው መቶ ክ/ዘ የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ሲሆን ተሰምተው በማይጠገቡ መንፈሳዊ ቃላቱ ምክሮቹና በቅድስና ሕይወቱ ይታወቃል፡፡ ጥንተ...
09/09/2025

በመንግስተ ሰማያት እንድታይን በዚህ ይቅርብሽ

ይህ ቅዱስ አባት የ4ኛው መቶ ክ/ዘ የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ሲሆን ተሰምተው በማይጠገቡ መንፈሳዊ ቃላቱ ምክሮቹና በቅድስና ሕይወቱ ይታወቃል፡፡ ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ በተጠቀሰው ዘመን በምድረ ግብጽ የምትኖር አንዲት ደግ ሴት ነበረች፡፡ አምላክ በፈቀደው ጋብቻ ውስጥ ገብታ ሰባት ወንዶች ልጆችን አፈራች፡፡ ሰባቱም ወንድማማቾች ገና ሕፃን እያሉ አባት በመሞቱ እናት ፈተና ውስጥ ገባች፡፡ ነገር ግን ብርቱ ሴት ነበረችና በወዟ ደክማ አሳደገቻቸው:: ሥጋዊ ማሳደጉስ ብዙም አይደንቅም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም እናቶች ይህንን ያደርጉታል ተብሎ ይታመናልና፡፡ የዚህች እናት የሚገርመው ግን ሁሉንም ንጹሐን፣ የተባረኩ፣ የክርስቶስ ወዳጆች፣ የቤተ ክርስቲያንም አለኝታዎች እንዲሆኑ አድርጋ ማሳደጓ ነው፡፡ ከሰባቱ ወንድማማቾች የመጨረሻው ባይሞን ወይም ጴሜን ይባላሉ፡፡ ለእነዚህም ዮሐንስ በኩር ሲሆን ባይሞን መቁረጫ ነው፡፡

ሰባቱም ወጣት በሆኑ ጊዜ ወገባቸውን ታጥቀው እናታቸውን ያገለግሉ፣ ለፈጣሪያቸው ይገዙ ነበር፡፡ ያየ ሁሉ እግዚአብሔር ከክፉ ጠላት ይጠብቃችሁ የሚላቸው፣ ቡሩካንም ሆኑ፡፡ አንድ ቀን ግን መንፈስ ቅዱስ በልባቸው ቅዱስ ሀሳብ አመጣና ለመመነን ወሰኑ፡፡ ይህንን ዓለም ከነ ኮተቱ ይተውት ዘንድ መርጠዋልና ወደ በርሃ ለመሔድ ተስማሙ፡፡ እናታቸው ምንም ያህል መንፈሳዊ ብትሆን የትኛዋም እናት ሁሉን ልጆቿን በአንዴ ማጣትን አትፈልግምና አላማከሯትም፡፡ ይልቁኑ እነርሱ ከሔዱ በኋላ እንዳትቸገር የምትታገዝበትን መንገድ አዘጋጅተውላት ተሰወሩ፡፡ ሰባት ልጆቿን በአንዴ ያጣችው እናት ብቻ አይደለችም፣ ሁሉም አዘነ፡፡ ተፈለጉ፣ ግን አየኋቸው የሚል ሰው አልተገኘም፡፡ ሰባቱም ቅዱሳን ከቤታቸው እንደ ወጡ ወደ ገዳም ሔደው አንዲት በዓት ተቀበሉ፡፡

ሰባቱም የሚጸልዩት፣ በጋራ የሚሠሩ፣ የሚመገቡ፣ የሚውሉ፣ የሚተኙም በጋራ ነው፡፡ በአገልግሎታቸውም ሆነ በፍቅራቸው አበውን ደስ አሰኙ፡፡ “እርስ በእርስ መዋደድ ከሁሉ ይበልጣል፡፡” እንዲሉ አበው፡፡ ከዘመናት ተጋድሎ በኋላ ግን ዝናቸው ከገዳሙ አልፎ በከተሞች ተሰማ፡፡ ይህንን የሰማችው እናታቸው የእርሷ ልጆች መሆናቸውን በማወቋ ፈጥና ወደ ገዳሙ ገሰገሰች፡፡ "ልያችሁ ልጆቼ?" ስትልም ላከችባቸው፡፡ እነሱ ግን "እናታችን በመንግስተ ሰማያት እንድታይን በዚህ ይቅርብሽ" አሏት፡፡ ምክንያቱም ሰባቱም የሴትን ፊት ላያዩ ቃል ገብተው ነበርና ይህ ለአንድ እናት ከባድ ቢሆንም እርሷ ግን ተረዳቻቸው፡፡ ፈጥናም ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ ከሰባቱ ቅዱሳን ደግሞ ትንሹ አባ ባይሞን የተለየ አባት ሆነ፡፡ ከንጽሕናው ቅድስናና ትጋቱ ባሻገር ከአንደበቱ የሚወጡ ቃላት ሕይወትነት ያላቸው ሆኑ፡፡

በዘመኑም ከሕፃን እስከ አዋቂ ድረስ ብዙዎች ከመንፈሳዊ ቃላቱ ተጠቅመዋል፡፡ እነዚህ ምክሮቹ ዛሬ ድረስ ለምዕመናንም ሆነ ለመነኮሳት ጣፋጮች ናቸው፡፡ እልፍ አእላፍ ከሆኑ ምክሮቹ ውስጥ ባልንጀራህ በወደቀ ጊዜ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥበት፡፡ ይልቅስ አንቃው፣ አበረታታው፣ ሸክሙንም አቅልለት እንጂ፡፡ ለጥሩ ባልንጀራህ የምታደርገውን ደግነት ለክፉው በእጥፍ አድርግለት፡፡ መድኃኒትን የሚሻ የታመመ ነውና፣ አልያ ግን ለበጐው ያደረከው ከንቱ ነው፡፡ ባልንጀራህ በበደለ ጊዜ አትናቀው፤ ያንተ ተራ በደረሰ ጊዜ ጌታህ ይንቅሃልና፡፡ የማንንም ኃጢአት አትግለጥ አታውራ፤ ካላረፍክ ጌታ ያንተኑ ይገልጥብሃልና፡፡ አንደበትህ የተናገረውን ሁሉ ለመሥራት ታገል፡፡” የሚሉት ይገኙበታል፡፡ ገዳማውያን በዚህ የቅዱሳን ቃል ተመርተው ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በታቸውን ስናጸና በረከታቸው ያድርብናል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ቴክኖ ኢትዮጵያ እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ እያለ በአዲሱ አመት የቴክኖ ስማርት ስልኮችን ከየትኛውም የሞባይል ሱቅ ሲገዙ ሽልማት የሚያስገኝ ኩፖን አብሮ መውሰዶን ...
09/09/2025

ቴክኖ ኢትዮጵያ እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ እያለ በአዲሱ አመት የቴክኖ ስማርት ስልኮችን ከየትኛውም የሞባይል ሱቅ ሲገዙ ሽልማት የሚያስገኝ ኩፖን አብሮ መውሰዶን አይርሱ! ከዛም በማህበራዊ ሚዲያ ማለትም በፌስቡክ፣ በኢንስታግራም እና በቲክቶክ ገጾት ፎቶዎትን ፖስት በማድረግ እና የቴክኖን ፔጅ ታግ በማድረግ ብዙ ላይክ ያገኘ ደንበኛችን ዛንዚባር ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ ቲኬት፣ ላፕቶፖች እና የቴክኖ ስማርት ስልኮችን ተሸላሚ ይሆናሉ፡፡ ታዲያ ምን ይጠብቃሉ ዛሬውን ይግዙ ይሸለሙ!!

Address

Bro
Washington D.C., DC
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Enawra - ኑና እናውራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share