Enawra - ኑና እናውራ

Enawra - ኑና እናውራ The best online entertainment for Ethiopians
(1)

08/18/2025

ሚካኤል የሥሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ “ማንነው እንደ እግዚአብሔር?” ማለት ነው፡፡

በክርስትና በአይሁድ፣ እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡

እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን በነገዱ ውስጥ በመላእክት ሁሉ ላይ በብዙ ክብር ሾመው፡፡ ይህም የከበረ መልአክ ክብር ይገባውና በጌታችን ፊት ስለ ሰው ልጆችና ስለ ፍጥረትም ሁሉ ይለምናል፤ ይማልዳልም፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ተአምራቱ ብዙዎች ናቸው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ለቅዱስ ሚካኤል የተሰጠውን ክብርና ባለሟልነት እንዲሁም የሠራቸውን ሥራዎች በስፋት እንመለከታለን፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ሁሉ ልዕልና ላይ ትሕትናን ደርቦ የያዘ በጸሎቱ ተማጽኖ በተራዳኢነት አምኖ ለሚለምነው ሁሉ ፈጥኖ በመድረስ ከአጋንንት ሠራዊተ ተንኰል የሚያድን ነው፡፡

በዘጸ.23÷20-22 “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአክህን በፊትህ እሰዳለሁ፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፤ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት፤ አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፣ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፣ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፣ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ፣ መልአኬ በፊትህ ይሄዳል” በማለት ለሙሴ ተናግሯል፡፡ ይህ ቃል ለሙሴና ለሕዝቡ ብቻ ተነግሮ ያበቃ ሳይሆን እስከዛሬና ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ ከሙሴ ጋር እንደነበረ ከእያሱ ጋር ደግሞ እንዲሁ መሆኑም ይህንን ያሳያል፡፡ በኢያሱ 5÷13 እንዲህ ይላል፡፡ “እንዲህም ሆነ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዓይኑን አንሥቶ ተመለከተ፡፡ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ ነበር፡፡ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን አለው፡፡ እርሱም አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ አለ፡፡

ኢያሱም ወደ ምድር በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደ፡፡ ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድን ነው አለው፡፡ የእግዚአብሔርም ሠራዊት አለቃም ኢያሱን አንተ የቆምህበት ሥፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን በፊቱ አውልቅ አለው፡፡ ኢያሱም እንዲሁ አደረገ” ይላል፡፡ ኢያሱ ከኢያሪኮ ጀምሮ ታላላቅ አሕዛብን አጥፍቶ እግዚአብሔር ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ የማለላቸውን የተስፋይቱን ምድር ለልጆቻቸው ያወረሳቸው በዚህ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ በተገለጸለት የእስራኤል መሪ በቅዱስ ሚካኤል እገዛ ነው፡፡ ከቃሉ እንደምንረዳው ከራሱ ወገን ወይም ከጠላቶቹ ወገን የሆነ አንድ ወታደር መስሎት ነበር፡፡ መልአኩ በሰው አምሳል ስለተገለጸለት አላወቀውም ነበር፡፡ ያነጋገረውም ያለ ፍርሃት ያለ ጭንቀት ያለድንጋጤ ወታደሮቹን እንደሚያነጋግር ዘና ብሎ ነው፡፡

ሆኖም “ከወገኖችህ ወይም ከጠላቶችህ አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ” ሲለው ኢያሱ በፊቱ የቆመው ከሙሴ ሳይለይ እስራኤልን የሚጠብቅ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን ሲረዳ ለመልአኩ ክብር መስጠት ስለሚገባ የአክብሮት ስግደት ሰገደለት፤ “ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድነው” በማለት በትህትና ጠየቀ፡፡ ጌታዬ ማለቱ የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጡር መስጠቱ መላእክት የጸጋ ጌቶች ይባላሉና፡፡ ኢያሱ መልአኩን ጌታዬ ብሎ ከጠራው እኛስ ጌታዬ፤ ቅዱስ ሚካኤል ለኔ ለባሪያህ ጸልይልኝ መጥተህ አድነኝ በማለት የአክብሮት የጸጋ ስግደት በመስገድ ብንለምነው፣ ብንታዘዘው ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አልወጣንም፡፡ መላእክትን ማክበርና መታዘዝ እንደሚገባ እግዚአብሔርም ነግሮናል፡፡ ይህን የተረዱ ገዳማውያን የመላእክትን ተራዳኢነት ተስፋ አድርገው ታምነው ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተካፋይ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የወንዶች ጉዳይ did it በዘነዘና …… በቅርብ ቀን በአዲስ ጉዳይ!
08/18/2025

የወንዶች ጉዳይ did it በዘነዘና …… በቅርብ ቀን በአዲስ ጉዳይ!

የሊቀ መላእክት  ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ እና ምልጃው አይለየን !!!ሚካኤል የሥሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ “ማንነው እንደ እግዚአብሔር?” ማለት ነው፡፡ በክርስትና በአይሁድ፣ እንዲሁም በመላዕክት ...
08/18/2025

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ እና ምልጃው አይለየን !!!

ሚካኤል የሥሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ “ማንነው እንደ እግዚአብሔር?” ማለት ነው፡፡ በክርስትና በአይሁድ፣ እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡ እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን በነገዱ ውስጥ በመላእክት ሁሉ ላይ በብዙ ክብር ሾመው፡፡ ይህም የከበረ መልአክ ክብር ይገባውና በጌታችን ፊት ስለ ሰው ልጆችና ስለ ፍጥረትም ሁሉ ይለምናል፤ ይማልዳልም፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ተአምራቱ ብዙዎች ናቸው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ለቅዱስ ሚካኤል የተሰጠውን ክብርና ባለሟልነት እንዲሁም የሠራቸውን ሥራዎች በስፋት እንመለከታለን፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ሁሉ ልዕልና ላይ ትሕትናን ደርቦ የያዘ በጸሎቱ ተማጽኖ በተራዳኢነት አምኖ ለሚለምነው ሁሉ ፈጥኖ በመድረስ ከአጋንንት ሠራዊተ ተንኰል የሚያድን ነው፡፡

በዘጸ.23÷20-22 “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአክህን በፊትህ እሰዳለሁ፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፤ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት፤ አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፣ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፣ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፣ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ፣ መልአኬ በፊትህ ይሄዳል” በማለት ለሙሴ ተናግሯል፡፡ ይህ ቃል ለሙሴና ለሕዝቡ ብቻ ተነግሮ ያበቃ ሳይሆን እስከዛሬና ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ ከሙሴ ጋር እንደነበረ ከእያሱ ጋር ደግሞ እንዲሁ መሆኑም ይህንን ያሳያል፡፡ በኢያሱ 5÷13 እንዲህ ይላል፡፡ “እንዲህም ሆነ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዓይኑን አንሥቶ ተመለከተ፡፡ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ ነበር፡፡ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን አለው፡፡ እርሱም አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ አለ፡፡

ኢያሱም ወደ ምድር በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደ፡፡ ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድን ነው አለው፡፡ የእግዚአብሔርም ሠራዊት አለቃም ኢያሱን አንተ የቆምህበት ሥፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን በፊቱ አውልቅ አለው፡፡ ኢያሱም እንዲሁ አደረገ” ይላል፡፡ ኢያሱ ከኢያሪኮ ጀምሮ ታላላቅ አሕዛብን አጥፍቶ እግዚአብሔር ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ የማለላቸውን የተስፋይቱን ምድር ለልጆቻቸው ያወረሳቸው በዚህ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ በተገለጸለት የእስራኤል መሪ በቅዱስ ሚካኤል እገዛ ነው፡፡ ከቃሉ እንደምንረዳው ከራሱ ወገን ወይም ከጠላቶቹ ወገን የሆነ አንድ ወታደር መስሎት ነበር፡፡ መልአኩ በሰው አምሳል ስለተገለጸለት አላወቀውም ነበር፡፡ ያነጋገረውም ያለ ፍርሃት ያለ ጭንቀት ያለድንጋጤ ወታደሮቹን እንደሚያነጋግር ዘና ብሎ ነው፡፡

ሆኖም “ከወገኖችህ ወይም ከጠላቶችህ አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ” ሲለው ኢያሱ በፊቱ የቆመው ከሙሴ ሳይለይ እስራኤልን የሚጠብቅ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን ሲረዳ ለመልአኩ ክብር መስጠት ስለሚገባ የአክብሮት ስግደት ሰገደለት፤ “ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድነው” በማለት በትህትና ጠየቀ፡፡ ጌታዬ ማለቱ የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጡር መስጠቱ መላእክት የጸጋ ጌቶች ይባላሉና፡፡ ኢያሱ መልአኩን ጌታዬ ብሎ ከጠራው እኛስ ጌታዬ፤ ቅዱስ ሚካኤል ለኔ ለባሪያህ ጸልይልኝ መጥተህ አድነኝ በማለት የአክብሮት የጸጋ ስግደት በመስገድ ብንለምነው፣ ብንታዘዘው ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አልወጣንም፡፡ መላእክትን ማክበርና መታዘዝ እንደሚገባ እግዚአብሔርም ነግሮናል፡፡ ይህን የተረዱ ገዳማውያን የመላእክትን ተራዳኢነት ተስፋ አድርገው ታምነው ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተካፋይ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የሊቀ መላእክት  ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ እና ምልጃው አይለየን !!!ሚካኤል የሥሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ “ማንነው እንደ እግዚአብሔር?” ማለት ነው፡፡ በክርስትና በአይሁድ፣ እንዲሁም በመላዕክት ...
08/18/2025

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ እና ምልጃው አይለየን !!!

ሚካኤል የሥሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ “ማንነው እንደ እግዚአብሔር?” ማለት ነው፡፡ በክርስትና በአይሁድ፣ እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡ እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን በነገዱ ውስጥ በመላእክት ሁሉ ላይ በብዙ ክብር ሾመው፡፡ ይህም የከበረ መልአክ ክብር ይገባውና በጌታችን ፊት ስለ ሰው ልጆችና ስለ ፍጥረትም ሁሉ ይለምናል፤ ይማልዳልም፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ተአምራቱ ብዙዎች ናቸው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ለቅዱስ ሚካኤል የተሰጠውን ክብርና ባለሟልነት እንዲሁም የሠራቸውን ሥራዎች በስፋት እንመለከታለን፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ሁሉ ልዕልና ላይ ትሕትናን ደርቦ የያዘ በጸሎቱ ተማጽኖ በተራዳኢነት አምኖ ለሚለምነው ሁሉ ፈጥኖ በመድረስ ከአጋንንት ሠራዊተ ተንኰል የሚያድን ነው፡፡

በዘጸ.23÷20-22 “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአክህን በፊትህ እሰዳለሁ፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፤ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት፤ አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፣ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፣ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፣ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ፣ መልአኬ በፊትህ ይሄዳል” በማለት ለሙሴ ተናግሯል፡፡ ይህ ቃል ለሙሴና ለሕዝቡ ብቻ ተነግሮ ያበቃ ሳይሆን እስከዛሬና ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ ከሙሴ ጋር እንደነበረ ከእያሱ ጋር ደግሞ እንዲሁ መሆኑም ይህንን ያሳያል፡፡ በኢያሱ 5÷13 እንዲህ ይላል፡፡ “እንዲህም ሆነ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዓይኑን አንሥቶ ተመለከተ፡፡ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ ነበር፡፡ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን አለው፡፡ እርሱም አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ አለ፡፡

ኢያሱም ወደ ምድር በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደ፡፡ ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድን ነው አለው፡፡ የእግዚአብሔርም ሠራዊት አለቃም ኢያሱን አንተ የቆምህበት ሥፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን በፊቱ አውልቅ አለው፡፡ ኢያሱም እንዲሁ አደረገ” ይላል፡፡ ኢያሱ ከኢያሪኮ ጀምሮ ታላላቅ አሕዛብን አጥፍቶ እግዚአብሔር ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ የማለላቸውን የተስፋይቱን ምድር ለልጆቻቸው ያወረሳቸው በዚህ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ በተገለጸለት የእስራኤል መሪ በቅዱስ ሚካኤል እገዛ ነው፡፡ ከቃሉ እንደምንረዳው ከራሱ ወገን ወይም ከጠላቶቹ ወገን የሆነ አንድ ወታደር መስሎት ነበር፡፡ መልአኩ በሰው አምሳል ስለተገለጸለት አላወቀውም ነበር፡፡ ያነጋገረውም ያለ ፍርሃት ያለ ጭንቀት ያለድንጋጤ ወታደሮቹን እንደሚያነጋግር ዘና ብሎ ነው፡፡

ሆኖም “ከወገኖችህ ወይም ከጠላቶችህ አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ” ሲለው ኢያሱ በፊቱ የቆመው ከሙሴ ሳይለይ እስራኤልን የሚጠብቅ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን ሲረዳ ለመልአኩ ክብር መስጠት ስለሚገባ የአክብሮት ስግደት ሰገደለት፤ “ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድነው” በማለት በትህትና ጠየቀ፡፡ ጌታዬ ማለቱ የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጡር መስጠቱ መላእክት የጸጋ ጌቶች ይባላሉና፡፡ ኢያሱ መልአኩን ጌታዬ ብሎ ከጠራው እኛስ ጌታዬ፤ ቅዱስ ሚካኤል ለኔ ለባሪያህ ጸልይልኝ መጥተህ አድነኝ በማለት የአክብሮት የጸጋ ስግደት በመስገድ ብንለምነው፣ ብንታዘዘው ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አልወጣንም፡፡ መላእክትን ማክበርና መታዘዝ እንደሚገባ እግዚአብሔርም ነግሮናል፡፡ ይህን የተረዱ ገዳማውያን የመላእክትን ተራዳኢነት ተስፋ አድርገው ታምነው ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተካፋይ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቀጥሎ አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ ነው፡፡ ለዘመነ ሰማዕታት መሪና አስተማሪ ነበር፡፡ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የሮም መንግስት ዓለምን በሮምና በ...
08/17/2025

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቀጥሎ አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ ነው፡፡

ለዘመነ ሰማዕታት መሪና አስተማሪ ነበር፡፡ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የሮም መንግስት ዓለምን በሮምና በአንጾኪያ ሲያስተዳድር የወቅቱ ንጉሥ ኑማርያኖስ ሲሆን የቤተ መንግስቱ ልዑላንና የጦር አለቆች ቅዱሳኑ ፋሲለደስና ሌሎችም ጠንካራ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ ንጉሱ ጦርነት ላይ ሲሞት ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ስልጣኑን ይዞ በሚገዛበት ሀገር ሁሉ ክርስቲያኖችን ምእመናን ማስገደልና ማሳደድ ጀመረ፡፡ ብዙ ሰማዕታትም ወደ ንጉሡ የሰማዕትነት አዳባባይ እየመጡ በጌታችን ስም ደማቸውን አፈሰሱ፡፡ ከእነዚህ ሰማዕታት አንዱ ቅዱስ ፋሲለደስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ ወደ ጌታችን ጸለየ፡፡ በመኝታውም ሳለ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ “በምድር አለቃ ሆነህ ሁሉን እንደምታዝ በሰማይም የክርስቶስ ወታደሮቹ የሆኑ የሰማዕታት አለቃ ሆነሃልና ደስ ይበልህ” አለው፡፡

በክንፎቹ ተሸክሞ ወደ ሰማይ አሳረገውና በጌታችን ፊት አቆመው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ፋሲለደስ ስለ ስሙ ይቀበል ዘንድ ስላለው መከራና በሰማይም ስለሚያገኘው ክብር ነገረው፡፡ ሰማዕትነት የሚቀበሉትንም ሁሉን ስማቸውን እየጠራ ነገረው፡፡ እርሱ ግን ከብዙ ተጋድሎ በኋላ ሰማዕት እንደሚሆንም አስረዳው፡፡ በሌሎቹ ሰማዕታትም ሆነ በእርሱ ላይ የሚደረስበትን መከራና በኋላም የሚያገኙትን ክብር ሁሉ በዝርዝር ነገረው፡፡ ታላቅ ቃልኪዳንም ገባለት፡፡ የሰማዕታትንና የቅዱሳንን መኖሪያ ካሳየው በኋላም ሰማዕትነቱን ሲፈጽም የሚያገኘውን ክብር መሆኑን ነግሮት በገነት ውኃ በመልአኩ እጅ እንዲጠመቅ ካደረገው በኋላ ወደ ምድር መለሰው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ብዙዎቹን ታላላቅ ሰማዕታት እጅግ አሠቃይቶ ክርስትናቸውን አንክድም ሲሉት በየተራ ገደላቸው፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስን ግን አምስት ከተማዎች ወዳሉበት አፍሪካ ላኩት፡፡

በዚያም ብዙ እጅግ ለስጋዊ ሰው ከባድ የሆኑ ሥቃዮች አደረሱበት፡፡ ከእርሱ ጋር ያመኑ ከ7 ሺህ በላይ ክርስቲያኖችንም ሰየፏቸው፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስንም ሰውነቱን በመንኰራኩር ፈጭተው በመጋዝ ሰነጣጥቀው ገደሉት፡፡ ነገር ግን ጌታችን ከሞት አስነሣው፡፡ እጅግ ብዙ አሕዛብም በአምላከ ፋሲለደስ አመኑ፡፡ ጣዖቶቻቸውንም ረገሙባቸው፡፡ መስከረም 9 ቀን 14ሺህ 737 የቅዱስ ፋሲለደስ ማሕበርተኞችን አንገታቸውን በሰይፍ ቆረጧቸው፡፡ ሰማዕትነታቸውንም ፈጸሙ፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስን ዳግመኛ በምጣድ ላይ አስተኝተው እሳት አነደዱበት፡፡ በተራራ ላይ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረው በዚያ ቀበሩት፡፡ አሁንም ጌታችን ከሞት አስነሥቶት በመኰንኑ ፊት እንዲቆም አደረገው፡፡ ንጉሡንም “አምላኬ ፍጹም ጤነኛ አድርጎ አስነሥቶኛልና እፈር፣ የረከሱ ጣዖቶችህም ይፈሩ” አለው፡፡ ሕዝቡም ይህን ተአምር ባዩ ጊዜ 2300 ሰዎች በጌታችን አምነው አንገታቸውን ተሰይፈው በሰማዕትነት ሞቱ፡፡

ቅዱስ ፋሲለደስንም ደግመኛ ሰውነቱን በመንኰራኩር ከፈጩት በኋላ በብረት ምጣድ ላይ አስተኝተው ከሥሩ እሳት አነደዱበት፡፡ ጌታችንም ከቁስሉ ፈውሶት ትልቅ ቃልኪዳን ሰጠውና ሰማዕትነቱን በትዕግስት እንዲፈጽም ነገረው፡፡ ንጉሡም አማካሪዎቹን ምን ማድረግ እንዳለበት ሲያማክራቸው “ፋሲለደስን ምንም ብናሠቃየው ሊሞት አልቻለም በእርሱም ምክንያት የሀገሩ ሰዎች ሁሉ አልቀዋልና ራሱን ቆርጠን ብንጥለው ይሻላል” አሉት፡፡ መኰንኑም ራሱን እንዲቆርጡት አዘዘና ቅዱስ ፋሲለደስ መስከረም 11 ቀን ሰማዕትነቱን ፈጸመ፡፡ 2007 የቅዱስ ፋሲለደስ ማኅበርተኞችም መስከረም 7 ቀን ዐረፉ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡ የዘመናችን ሰማዕታት ገዳማውያን ናቸው፡፡ ዓለምንና አምሮቷን ትተው መንነዋልና፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጻናበረከታቸው ያድርብናል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

08/16/2025

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ እና ምልጃው አይለየን !!!

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ከቀስት እናመልጥበት ዘንድ የተሰጠን ምልክታችን መስቀል በብሉይ የወንጀለኞች መቅጫ ቢሆንም ለዓለም መዳኛነት መርጦታልና ትንቢት ሲነገርለት፣ በበርካታ ምሳሌዎች ሲገለጥ ኖሯል፡፡ የሰው ልጅ ራሱ...
08/16/2025

ከቀስት እናመልጥበት ዘንድ የተሰጠን ምልክታችን

መስቀል በብሉይ የወንጀለኞች መቅጫ ቢሆንም ለዓለም መዳኛነት መርጦታልና ትንቢት ሲነገርለት፣ በበርካታ ምሳሌዎች ሲገለጥ ኖሯል፡፡ የሰው ልጅ ራሱ አርአያ ትዕምርተ መስቀል ነው፡፡ ይስሐቅ ሊሰዋ ሲሔድ የተሸከመው እንጨት፣ ቅዱስ ያዕቆብ ያያት የወርቅ መሰላል፣ ባሕረ ኤርትራን የከፈለችው የሙሴ በትር፣ የነሐሱ እባብ የተሰቀለበት እንጨትና ሌሎች ምሳሌዎችን የትርጓሜ መምሕራን ይነግሩናል፡፡ ይህም ቅዱስ መስቀሉ ጌታችን ለሰው ልጅ ፍጹም ፍቅሩን ሲገልጽበት፣ ሥጋውን ሲቆረስበት፣ ደሙን ሲያፈስበት፣ በምክንያት እደሆነ ያሳየናል፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም በኅቱም ድንግልና ተወልዶ፣ በፈቃዱ መከራ መስቀልን ተቀብሎ፣ ከሰይጣን ባርነት፣ ከኃጢአት ቁራኝነትም አድኖናል:: ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 59÷4 "ለሚፈሩሕ ከቀስት ያመልጡ ዘንድ ምልክትን ሰጠሃቸው" በማለት መስቀሉን በትንቢት ይገልጸዋል፡፡

ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ዻውሎስ (በ1ኛ ቆሮ 1÷18 እና በገላ 6÷14) ስለ መስቀሉ አምልቶ አስፍቶ ጽፏል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም "ከነገር ሁሉ የሚበልጠው መስቀል ከጠላታችን ያደነናል" ይለናል፡፡ እኛም ለመስቀሉ የጸጋ ስግደት እንሰግዳለን፣ እናመሰግነዋለን፣ እናከብረዋለን፤ አምነን ከብረን እንኖራለን፡፡ አባቶቻችን በመስቀሉ ምርኩዝነት የኃጢአት ማዕበልን፣ ባሕረ እሳትን ተሻግረዋል፣ አጋንንትን ድል ነስተዋል፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል ተአምራትን ሲያደርግ አይሁድ በምቀኝነት ለሦስት መቶ ዓመት ቀብረው አጥፍተውታል፡፡ በዚህም ምክንያት የጻድቁ የሮም ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት ንግስት እሌኒ ልጇ ክርስቲያን ከሆነ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን ልትፈልግ ለእግዚአብሄር ተስላ ነበር።

ልጇ አምኖ ሲጠመቅም ብዙ ሰራዊት አስከትላ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች፡፡ ስለ ከበረው መስቀል የሚያስረዳት ግን አላገኘችም፡፡ የአይሁድ ወገን የሆነ አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊም አስራ ስታስጨንቀው የጎልጎታ ኮረብታ ላይ ተቀብሯል ተብሎ ሲነገር እንደሰማ ነገራት፡፡ አይሁድ የከበረ መስቀሉን በቀበሩበት ስፍራ ሦስት የቆሻሻ ተራሮች ነበሩና የትኛው ላይ እንደተቀበረ ለማወቅ መስከረም 16 ደመራ ደምራ ስታቃጥለው የእጣኑ ጢስ መስቀሉ ያለበትን ስፍራ አመለከታት፡፡ መስከረም 17 ቀንም ከሁለት መቶ ዓመት በላይ የተቀበረው መስቀል ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት 10 ቀን ሶስት መስቀሎች ተገለጡ፤ ነገር ግን የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የትኛው እንደሆነ አላወቁም ነበር።

በገቢረ ተአምራት ለመለየትም የሞተ ሰውም አመጡና መስቀሉን ሲያደርጉበት ተነሳ እሌኒም የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደችለት የክርስቲያንም ወገኖች ሁሉ ሰገዱለት። ከዚህም በኃላ ለቅዱስ መስቀሉና የሚሆንና ሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት አነፀች። ለበረከት እንዲሆናትም ጥቂት ወስዳ ወደ ሀገሯ ተመለሰች፡፡ በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን የፋርሱ ንጉስ መጥቶ ኢየሩሳሌምን አጠፋት የከበረ መስቀሉንም ይዞ ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ። የሮም ንጉስ ህርቃልም ወደ ፋርስ ዘምቶ ድል ነሳቸው፤ የከበረ እፀ መስቀሉንም ጥቂት ለበረከት ወስዶ ወደ ኢየሩሳሌም መለሰው፡፡ የክርስትናው ዓለም ይህን እጸመስቀል ለአራት ሲከፋፈለው የእስክንድርያ ድርሻ በ15ኛ መቶ ክፍለ ዘመን በአፄ ዳዊት ወደ ሃገራችን መጥቶ በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ አማካኝነት በግሸን ማርያም ደብረ ከርቤ ተቀምጧል፡፡ ገዳማውያንም በመስቀሉ ኃይል ዘወትር የጠላትን ኃይል ድል ይነሱበታልና ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና በረከታቸው ያድርብናል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

08/15/2025

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ የበደሉትንም ያልበደሉትንም ሞት ገዛቸው” እንዳለ አዳምና ሔዋን ብቻ ያይደሉ ከእነርሱ የተወለዱ ልጆችና የልጅ ልጆቻቸው ሁሉ በደለኞች ሆኑ፡፡

የመጀመሪያውና ታላቁ በደል ጥንተ አብሶ ሲሆን ቅዱስ ቄርሎስ “ጥንተ ኃጢአት” ቅዱስ ሳዊሮስና ቅዱስ ኤፍሬም “ዘቀዳሚ መርገም” ብለውታል። ይህም የውርስ ኃጢአት ከአዳም ጀምሮ ከወላጅ ወደ ልጅ እየተላለፈ ሰውን ሁሉ የሚገዛ ሆነ። ባሕርየ ሰብእ ጐሰቈለ፣ ንጽሐ ጠባይዕ አደፈ፣ ኃጢአት ብዙዎችን አጠመደች፡፡ ስለዚህም ተላልፈው ለሞትና ለሲኦል ተሰጡ። ከዚህ ንጽህት ሆና የተገኘች ቅድስት ድንግል ማርያም ብቻ ናት፡፡

በኃጢትም ምክንያት በባሕርየ ሰብእ ጸንቶ የነበረውን መርገም ሊያጠፋ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ሰው ሆኖ በሚጸነስበት ልክና ሥርዓት ከንጽሕት ድንግል ማርያም ተወለደ።

ፍጹም ጌታ ፍጽምት በሆነች በእመቤታችን ማኅፀን አደረ፣ ቡሩክ አምላክ “ከሴቶች ይልቅ አንቺ ቡርክት ነሽ” ተብላ በመልአኩና በኤልሳቤጥ አንደበት ከተመሰገነች ከድንግል ተወለደ፤ ቡርክት ማኅፀን የቡሩክ አምላክ ማደሪያ ሆነች፡፡ ቅድስት ማኅፀን ቅዱስ ጌታን በሥጋ አስገኘች፤ ከመርገም በፊት ከነበረች ቡርክት ምድር አዳም ያለእናት ያለአባት ተፈጠረ፤ ዳግማይ አዳም ክርስቶስም ኃጢአተ አዳም ከሌለባት ቡርክት ማርያም ተወለደ፤ ከድንግል የተወለደ ጌታ ነውር ነቀፋ የሌለበት ንጹህ እንደሆነ፣ የወለደችው ድንግልም ነውር ነቀፋ የሌለባት ንጽህት ናት፤ እርሱ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ቅዱስ እንደሆነ እርሷም በጊዜ ሁሉ ቅድስት ናት፡፡ ለመወለዱ ዘርዕ ምክንያት አልሆነውም፤ በንጽሕና በቅድስና ጸንታ ከኖረች ከድንግል ያለአባት ተፀነሰ፤ ሕማም፣ ድካም ሳያገኛት በሴቶች የሚደርሰውም ሳይደርስባት ተወለደ እንጂ።

በባሕርየ መለኮቱ ጽድቅ እንጂ ኃጢአት፣ ሕያውነት እንጂ መዋቲነት የማይስማማው አምላክ እናት ትሆነው ዘንድ ከሴቶች መካከል መርጦ፣ ትህትናን እንደ ዝናር አስታጥቆ፣ ንጽህናን እንደ አክሊል አቀዳጅቶ፣ ካዘጋጃት ከቅድስት እናቱ ነፍስና ሥጋን ነሣ፡፡ የነሣውንም ሥጋ በተዋህዶ ከባሕርየ መለኮቱ ጋር አንድ አደረገው። ሥጋን ተዋህዶ ስለተወለደ ግን በባሕርየ ሰብእ ፀንቶ የነበረ መርገመ ሥጋ አላገኘውም፤ ድንግልም ኃጢአተ አበው የሚቆራኘው ተራ ሰውን የወለደች አይደለችም፡፡ የዚህ ዓለም ርኲሰት እንዳያገኛት ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ የጠበቃት ንጽህት እንደመሆኗ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሳለው ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ተብሎ የሚመሰገን የቅድስናው መጠን የንጽህናው ልክ የማይሰፈር የማይለካ ፍጹም ጌታን ወለደች እንጂ።

ቅዱስ ዲዮናስዮስ በሃይማኖተ አበው 101÷14 “አምላክን የወለደች አደፍ ጉድፍ የሌለባት ንጽህት በሆነች በድንግልማርያም ማኅፀን አደረ” መሆኗን ይነግረናል፡፡ ሌላው ታላቅ አባት ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ በዚሁ መጽሐፍ 35÷12 “መጀመሪያ የሌለው እርሱ አደፍ ጉድፍ የሌለባት ንጽህት ከሆነች ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም የነሣውን መገኛ ያለውን የሥጋ ባሕርይ ተዋሀደ” ይለናል፡፡ ከድንግል የተወለደ ክርስቶስ ኢየሱስ በሰው የተፈረደውን መከራ ተቀብሎ ሰውን ለማዳን ሰው ቢሆንም ቅሉ ዕድፈት ርኲሰት ያላገኘው ንጹህ ቅዱስ እንደሆነ አምላክን የወለደች ቅድስት ድንግል ማርያምም እድፈት ርኲሰት የሌለባት ንጽህት ቅድስት መሆኗን እንረዳለን። ይህን ንጽህናዋን የተረዱ ገዳማውያን ዘወትር በውዳሴዋና በቅዳሴዋ ሰዓሊ ለነ ቅድስት ይሏታል፡፡ ገዳማቸውን ሰንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና በረከቷ ያድርብናል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ሕጻኑም ሦስት ነገሮች ያስፈሩኛል በማለት ማልቀስ ጀመረኤፍራጥስ በተባለች መንደር በ451ዓ.ም ተወለደ። አባቱ የሦርያ ሊቀ ካህናት ነው። ከእርሱ በቀር ልጅ አልነበረውም። የሥሩግ ኤጲስ ቆጶስ ...
08/15/2025

ሕጻኑም ሦስት ነገሮች ያስፈሩኛል በማለት ማልቀስ ጀመረ

ኤፍራጥስ በተባለች መንደር በ451ዓ.ም ተወለደ። አባቱ የሦርያ ሊቀ ካህናት ነው። ከእርሱ በቀር ልጅ አልነበረውም። የሥሩግ ኤጲስ ቆጶስ የነበረው ቅዱስ ያዕቆብ ወይም ከ366 – 438 ዓ.ም የኖረ አባት ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ። ያዕቆብ ማለት አኃዚ፣ አዕቃጺ ማለት ወይም ሰኮና የሚይዝ ማለት ነው፡፡ በ3 ዓመቱ እናቱ ይዛው ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሄደች። በዕርገት ቊርባን ጊዜ ከእናቱ ተለይቶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ። ሊቀ ጳጳሱ ጸጋ እግዚአብሔር እንደጠራቸው ዐውቆ በጽዋው 3 ጊዜ ከደሙ አጠጣው። ብላቴናው ያዕቆብም በሕዝቡ ፊት ”3 ነገሮች ያስፈሩኛል“ በማለት ማልቀስ ጀመረ። ጳጳሱና ሕዝቡ ወደ ሕጻኑ ያዕቆብ ቀርበው "ምን ምን?" አሉት፡፡ እርሱም ነፍሴ ከሥጋየ ስትለይ፣ ቅድመ እግዚአብሔር ለፍርድ ስቀርብ፣ በእኔ ላይ ከፈጣሪየ የፍርድ ቃል ሲወጣ" አላቸው፡፡ ሕዝቡና ካህናቱ ይህንን ሲሰሙ “እግዚአብሔር በሕፃኑ አድሮ ገሠጸን ” በማለት ማልቀስ ጀመሩ።

ቅዱስ ያዕቆብ የተማረው በኤዴሳ ነው። ኤዴሳ የዛሬዋ ቱርክ ከተማ ነበረች። የዛሬን አያድርገውና ጥንተ ክርስትና የተሰበከባት የክርስትና ማዕከል ነበረች። ኤዴሳ በቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ደግሞ ”ሮሐ“ በሚል ስያሜ ትታወቃለች። ዛሬ ግን ኡርፋ በመባል ትጠራለች። ቅዱስ ያዕቆብ በሰባት ዓመቱ የብሉያትና ሐዲሳት መጻሕፍትን አጥንቷል። በአስራ ሁለት ዓመቱ ድርሰት መድረስ ችሏል። አንድ ቀን አምስት ያህል ጳጳሳት መጥተው ቅዱስ ያዕቆብን “ከፊታችን ቆመህ እኛ እየሰማህን አዲስ ድርሰት ድረስልን” አሉት። ቅዱስ ያዕቆብም ትሕትና ልማዱ ስለሆነ “አባቶቼ በእናንተ ፊት እንኳን እንግዳ ድርሰት መድረስ ያጠናሁትን ቀለም አከናውኖ መናገር አይቻለኝም” አላቸው። “እንግዲያውስ በቤተ ክርስቲያን ያለውን ሥዕል አርባዕቱ እንሰሳ ተርጉምልን” አሉት። ነቢዩ ቅዱስ ሕዝቅኤል በኮባር ወንዝ እንዳያቸው ሆነው አንገታቸውን ዘንበል ዘንበል አድርገው ተሥለዋል።

ቅዱስ ያዕቆብም ይህንንስ ይሁን ብሎ “ሁለት ክንፋቸው ወደ ታች ማድረጋቸው ደኃራዊነቱን ይመረምሩታል፤ ያጡታል። ሁለት ክንፋቸው ወደ ላይ ማድረጋቸው ቀዳማዊነቱን ይመረምሩታል፤ ያጡታል፡፡ ሁለቱን ክንፋቸውን ወዲያና ወዲህ ማድረጋቸው ጽንፍ እስከ ጽንፍ ምልዓቱን፣ ስፋቱን ይመረምራሉ፤ ያጡታል። የማይመረመር ስለሆነ ስለዚህ ዕፁብ ዕፁብ ዕፁብ ይላሉ። ብሎ ተርጉሞላቸዋል። ለረጅም ዓመታት አነስተኛ የሆነችውን የሥሩግ ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስን በመጎብኘት ያገለግል ነበር። በ519 ዓ.ም በባትናም ኤጲስ ቆጶስነት ተሹሞ ሁለት ዓመት ከመንፈቅ አገልግሎ ዐርፏል። ዕረፍቱም ሰኔ 27 ነው። ገድል ተጽፎለታል፣ ጽላት ተቀርጾለታል። በሦርያ ቋንቋ በመቶዎች የሚቆጠሩ በግጥም መልክ የተዘጋጁ ድርሳናትን፣ በመጻፍ “ዕንዚራ መንፈስ ቅዱስ“ የመንፈስ ቅዱስ ዋሽንት የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

በስሙ የሚታወቅ ቅዳሴም ደርሷል። በሀገራችን በቅዱሳን መላእክት በዓላትና በነገረ ምጽአት መታሰቢያ ዕለት ቅዳሴው ይቀደሳል። ስለ ነገረ ድኅነት በስፋት አስተምሯል። ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በግጥም መልክ የተዘጋጀ ድርሰት ደርሷል። ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ የመለኮትና የሰውን ፍጹም ተዋሕዶ በማስተማሩ “የተዋሕዶ ጠበቃ “ተብሏል። የንስጥሮስንና በ451 ዓ.ም የተካሔደውን የኬልቄዶን ጉባኤ የምንታዌ ትምህርትም አውግዟል፡፡ ይህን የቅዱሳን የሃይማኖት መሠረት የያዙ ገዳማውያንም በእምነት ጽናት፣ በጾምና በጸሎት ትጋት ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን በመደገፍ በዓቸውን በማጽናት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

08/14/2025

የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤቷ እና ምልጃዋ አይለየን !!!

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

Address

Washington D.C., DC

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Enawra - ኑና እናውራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share