06/15/2025
ባህራን እንዲሞት ከተጣለበት ባህር በደህንነት ወጥቶ የመልካም ሰው ልጅ ሆኖ አደገ፣ ወደ ባህር የጣለውንም ሰው ሀብት ወርሶ የጠበቀው አባቱ ቅዱስ ሚካኤልን እየዘከረ በስሙ ለንዳያን እየመጸወተ፣ አቢያተ ክርስቲያናትን እያሳነጸ ኖረ።
ቅድስት አፎሚያ ባሏ አስተራኒቆ ሊያርፍ ሲል እንዲያደርግላት የለመነችው የመጨረሻው ነገርብየቅዱስ ሚካኤልን ስዕል በሰሌዳ እንዲያሰራላት ነው። በዚያ ስዕልም ዲያብሎስን ሁለት ጊዜ አሳፍራ መልሳዋለች። በመጨረሻም ያላትን ሁሉ ለነዳያንና ለቤተክርስቲያን ማሰሪያ ሰጥታ አርፋለች።
ታላቁ አለቃ ሺ በክንፉ፣ ሺ በአክናፉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ለወዳጆቹ ፈጥኖ ደራሽ ደግ አባት ነው። ውለታው የበዛላቸው እናቶቻችን ደግሞ በታቦታት ንግስ ጊዜ ፡-
"ቅዱስ ሚካኤል ለወደደው
ከእሳት ያወጣል ከነደደው!!!" እያሉ ይዘምሩለታል።
ዘማሪ አቤል መክብብም በጥዑም ዜማ
"በሔድኩበት ሁሉ ከአፌ አትነጠልም
የማር ወለላ ነው ሚካኣል ያንተ ስም!!!" ሲል ውለታውን ያወሳል።
"ማር ሚካኤል ልበል" አዲስ መዝሙር በቅርብ ቅን በማህቶት ቲዩብ።