Nigat ንጋት

Nigat ንጋት Nigat Digital Creator!

( ማንም አሸነፈ ማን በማይመለከተን  )  የአሜሪካን ምርጫ ቅስቀሳ ካማላ ሃሪስን ደግፎ በዚህ ካምፔን እየተሳተፈ  ያለው ባራክ ኦባማ ፡. ..  ዶናልድ ትራምፕ በአንዳንድ የሙስሊም ሀገራት ...
11/02/2024

( ማንም አሸነፈ ማን በማይመለከተን ) የአሜሪካን ምርጫ ቅስቀሳ ካማላ ሃሪስን ደግፎ በዚህ ካምፔን እየተሳተፈ ያለው ባራክ ኦባማ ፡. .. ዶናልድ ትራምፕ በአንዳንድ የሙስሊም ሀገራት ላይ የጉዞ እገዳ ማድረጋቸውን አውግዞ ሲናገር ተሰምቷል ።....
አስባችሁታል ? ኦባማ ኢራቅን በቦንብ ማረሱን ፡ ሶሪያ ላይ የቦንብ ውርጅብኝ ማዝነቡን ረስቶ. .. ታሊባንን በመምታት ሰበብ አፍጋኒስታን በቦንድ እንዳላጋያት ሁሉ. .....
ያችን የአረብ ምድር ገነት ተብላ የሚቀናባትን ሊቢያን ከተሞቿን በቦንብ አውድሞ ወደፍርስራሽነት የለወጠው ሶዬ. .. ....

ሰላማዊቷን የመንን አገር እስከማትመስል ድረስ ቦንብ እንዳላዘነበባት ፡ እዚህ ጎረቤት ሶማልያን ሳይቀር በጀት የደበደበ ፡ ይህ ርህራሄ የለሽ መሪ ። ....
ይህ ጨካኝ ፕሬዝደንት ፡ በስልጣን በቆየባቸው ስምንት አመታት ፡ በነዚህ የሙስሊም ሀገራት ላይ በሺህ የሚቆጠሩ ንፁሃን በቦንብ እንዲገደሉ ያደረገ ሰው ፡ ይህንን ወንጀሉን ረስቶ ፡ ሙስሊሙን ለምርጫ ቅስቀሳ ሲያውል ፡ መስማት ያናድዳል ።

Via wasihun

በእስራኤል የማያቋርጥ የአየር ድብደባ የተገደሉት የፍልስጤም ህፃናት ቁጥር ከ 1,000 በልጧል ። በ 21ኛው ክፍለዘመን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ህፃናት የሚሳኤል ጥቃት ኢላማ ተደርገው በአ*ረ...
10/17/2023

በእስራኤል የማያቋርጥ የአየር ድብደባ የተገደሉት የፍልስጤም ህፃናት ቁጥር ከ 1,000 በልጧል ።
በ 21ኛው ክፍለዘመን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ህፃናት የሚሳኤል ጥቃት ኢላማ ተደርገው በአ*ረ መኔዋ ሀገር እየተጨፈጨፉ ነው ።

አሜሪካና አጋሮቿ ምእራባውያንም እስራኤልን " አይዞሽ በርቺ " ማለታቸውን ቀጥለውበታል ። ፍልስጤማዊያን በዚያች ጋዛ በምትባል የቁም እስርቤት ከሰማይ የሚወርድባቸውን እሳት ወደየትም ሳይሄዱ እየተቀበሉት ነው ። በየፍርስራሹ ያሉት ንፁሀን ፍልስጤማዊያን አስክሬንና ቁስላቸው ሳይነሳ ከላይ ሌላ ሚሳኤል እየዘነበባቸው የምድርን አስቃቂውን ህይወት እያሳለፉት ነው ።

እዚያች እስርቤቷ ጋዛ አሁን የሚበላ የለም ! የማጠጣ የለም ! ህክምና የለም ! መሸሺያ መደበቂያ የለም ! ከአለም መገናኘት የለም ! ኢንተርኔት ስልክ የለም ! መተኛት ማረፍ የለም ! ሁሉም የለምምም !!!!

እዚያ ያለው እንደጎርፍ የሚፈስ የንፁሀን ደም ነው !
እዚያ ያለው እንደ ዝናብ የሚዘንብ የእሳት ሚሳኤል ነው !
እዚያ ያለው የህፃናት ዋይታና ለቅሶ ነው !
እዚያ ያለው የሴቶችና አዛውንቶች እንባ ነው !!

ብቻቼውን ሆነው ምናልባትም ኢራን ብቸኛ እረዳታቸው ሆና በመላው ምእራባውያን የምትደገፈውን ፅዮናዊቷን እስራኤልን ለመታገል የሚቀበሩበት እንኳን መሬትን ለማስቀረት ሁሉን ነገር ከፍለው የቻሉትን ታገሉ ። መሳሪያም ገንዘብም አጋዥም ሳይኖራቸው በህይወታቸው የአላህን እርዳታ ብቻ ተማምነው የቻሉትን አደረጉ ያሳኩትን አሳክተው የከፈሉትን ከፈሉ እየከፈሉም ነው !!!

ግና የገጠሟት እስራኤልና አጋዦቿ ከነርሱ አቅም አንፃር ምናልባትም ሚሊዮን እጥፍ የሚልቅ አቅም ያላቸው ናቸውና መስዋዕትነቱ እጅግ መራር እጅግም አሳዛኝ ነው ።

ፍርደገምድሉ አለምም የፍልስጤማውያንን እልቂት በዝምታ ሲከታተል ምእራባውያን በደስታ እያጣጣሙት ነው !
ብቻ የአላህ እርዳታ ይመጣላቸው ይሆን ብለን ተስፋ ከማድረግ ውጭ ምን ማድረግ እንችል ይሆን 😢

የማይገባንና የኛ ያልሆነውን   አልመን አናውቅም ።  የምንፈልገውም ቢሆን በምክክር እና ሰጥቶ በመቀበል እንጂ በሃይል መሻታችንን በሌሎች ላይ የመጫን ዕቅድና ፍላጎት ከቶውንም የለንም።ለምን ...
10/14/2023

የማይገባንና የኛ ያልሆነውን አልመን አናውቅም ። የምንፈልገውም ቢሆን በምክክር እና ሰጥቶ በመቀበል እንጂ በሃይል መሻታችንን በሌሎች ላይ የመጫን ዕቅድና ፍላጎት ከቶውንም የለንም።ለምን ቢባል ? የሰው ወርቅ አያደምቅማ! ምንስ ጎድሎብን? የትየለሌ የቁሳዊ እና ሰብዓዊ ሀብት አለን። ከፈጣሪ ቀጥሎ የሚተጉ ጀግኖች የማይነጥፉበት ሀገር አለችን። አኩሪ አሻራ የሚያኖር መሪም አለን። የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር ስክነት፣ የሌሎችን ህመም እንደራስ መረዳት፣ አላፊ ችግሮችን በመተው ለነገው ብሩህ ተድላ መስዋዕትነት መክፈል፣ ለጋራ ጥቅም አብሮ መቆም ነው። ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚቻለው ብሔራዊነትን በቆራጥ አርበኝነት በማፅናት ነው።

🇮🇱               🇵🇸እስራኤል - 1,300 ተገድለዋል, 3,418 ቆስለዋልጋዛ - 1,900 ተገድለዋል፣ 7,696 ቆስለዋል (በእስራኤል ውስጥ በግምት 1,500 የሃማስ ተዋጊዎች ተገድ...
10/14/2023

🇮🇱 🇵🇸

እስራኤል - 1,300 ተገድለዋል, 3,418 ቆስለዋል

ጋዛ - 1,900 ተገድለዋል፣ 7,696 ቆስለዋል (በእስራኤል ውስጥ በግምት 1,500 የሃማስ ተዋጊዎች ተገድለዋል)

ዌስት ባንክ - 52 ተገድለዋል ፣700 ቆስለዋል

ሊባኖስ - 6 ተገድለዋል

በተባበሩት መንግስታት ግምት መሰረት በአሁኑ ጊዜ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ፍልስጤማውያን ተፈናቅለዋል።

Today's best photoI bet haters gone say fake news… Oh well 😂deal with it!
10/06/2023

Today's best photo
I bet haters gone say fake news… Oh well 😂deal with it!

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የግብር መክፈያ ጊዜ እንዲራዘም ወሰነ *********************** የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ...
07/07/2023

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የግብር መክፈያ ጊዜ እንዲራዘም ወሰነ
***********************

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ወቅታዊ ተግዳሮቶችን ከግምት በማስገባት የግብር መክፈያ ጊዜ እንዲራዘም ወስኗል።

በዚህም መሠረት የግብር መክፈያ ጊዜ እስከ መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ.ም እንዲራዘም እንዲሁም ንግድ ፍቃድ የማደሻ ጊዜ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲራዘም ውሳኔ አሳልፏል።

ከጦርነቱ በፊት በሥራ ላይ የነበሩ የተለያዩ የኮንትራት ውሎች (የውኃ፣ የመንገድ እና የሕንፃዎች) ጥናትን መሠረት በማድረግም ውላቸው እንዲታደስ መወሰኑን ከክልሉ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

 በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን  ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም  ወደ ትግራይ  ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባስተላለ...
07/05/2023



በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ 13 አባላት ያሉት የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ .ም ወደ ክልል ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል።

ልዑካን ቡድኑ ወደ መቐለ የሚጓዘው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሰረት ለትግራይ ክልል እንዲሰጥ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስና በትግራይ ከሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በሰላም ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር መሆኑ ታውቋል።

ይህንን በተመለከተም ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት የተላከው ደብዳቤ ለፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት ዛሬ ማለዳ እንዲደርስ ተደርጓል።

መረጃው የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

"ሰርጎ ገብ ፖለቲካ መነሻና ፈርጅ አለው። መነሻው አክራሪነት፣ ዓይነተ ብዙ ጽንፈኝነት (የብሔር፣የሀይማኖት፣ የፖለቲካ ...ወዘተ)፣ ልጓም አልባነት፣ ራስ ወዳድነት፣ የተናጠል እውነት ሽኩቻ ...
06/21/2023

"ሰርጎ ገብ ፖለቲካ መነሻና ፈርጅ አለው። መነሻው አክራሪነት፣ ዓይነተ ብዙ ጽንፈኝነት (የብሔር፣የሀይማኖት፣ የፖለቲካ ...ወዘተ)፣ ልጓም አልባነት፣ ራስ ወዳድነት፣ የተናጠል እውነት ሽኩቻ (የተራብኩ እኔ፣ የተጠማው እኔ የተገፋው እኔ ...እኔ ማለት)፣ ያልተገባ ጥቅምና ክብር ፍለጋ፣ በትላንት እስረኛ መሆን፣ አዲስ ባህል የመላመድ ችግር ሲሆኑ ፈርጆቹ መከፋፈል፣ መጠላላት፣ መጠላለፍ፣ መገፋፋት አልፎም መገዳደል ናቸው።

የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት
ዶ/ር አቢይ አህመድ

የአማራ ሕዝብ ለዘመናት ተፈርጆ (demonized) ተጠቅቷል፤ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፤ አሁንም ቢሆን ዙሪያገባውን በስጋት ውስጥ ይገኛል። 1983 ዓ/ም ጠላቶቹ ተሰባስበው ከጫኑበት "የአሸና...
04/07/2023

የአማራ ሕዝብ ለዘመናት ተፈርጆ (demonized) ተጠቅቷል፤ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፤ አሁንም ቢሆን ዙሪያገባውን በስጋት ውስጥ ይገኛል። 1983 ዓ/ም ጠላቶቹ ተሰባስበው ከጫኑበት "የአሸናፊዎች ፍትኅ" ገና አልተላቀቀም፤ ስርዓታዊና መዋቅራዊ ጥቃቶቹ እንዳሉ ቀጥለዋል። ባጭሩ እስካሁን ያለበት አጠቃላይ ሁኔታ "ከ1983 ዓ.ም እስከ 1983 ዓ.ም" ነው!

የጠላት ዋና አቅም ምስለኔ ነው፤ ዱሮም ሕዝቡ ትጥቁን የተቀማው በተመሳሳይ አግባብ ነበር። በ1983 ዓ/ም ትጥቁን የተቀማው የአማራ ሕዝብ 2013 ዓ.ም ላይ በተዘረፈ ጠመንጃ ወረራ ተፈፅሞበታል!

ሆኖም በሂደት የአማራ ሕዝብ በጦርነት ውስጥ መስዋዕትነት እየከፈለ መደራጀቱና መታጠቁ አልቀረም። ይሄም የስጋት ምንጭ ተብሎ ታሪክ ራሱን ደግሟል።

የሆነ ሆኖ የአማራ ሕዝብ ከጉዳቱ ገና ሳያገግም እና ሀገራዊ ፖለቲካው ስንዝር ሳይራመድ እንዲሁም ቅንጣት ሀገራዊና አካባቢያዊ መተማመን ሳይፈጠር "የብቻ ተፈራጅ፣ለብቻ ትጥቅ አውራጅ" የሚባል አዋጅ አሁን ተቀባይነት የለውም።

መጀመሪያ ሀገራዊ ችግሮችንና ተቃርኖዎችን በውይይት እና በሰለጠነ ድርድር መፍታት ይቀድማል። ሁሉም ዜጎችና ሕዝቦች እኩልና ነፃ መሆን አለባቸው። ሁሉንም ኢትዮጵያውያን አሸናፊ የሚያደርግ ፍትኃዊ ስርዓት እውን ሊሆን ይገባል።

የበርካታ አሻጥሮችና ጥቃቶች ሰለባ የሆነና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት እንዲሁም ከፍተኛ ስጋት የተጋረጠበት ሕዝብ "ልዩ ኃይል" ብቻ ሳይሆን "ልዩ ልዩ ኃይሎችም" ያስፈልጉታል።

ያው በአቦሸማኔ ጥድፈት ረጂም ርቀት መጓዝ አይቻልም!

መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት  አቅጣጫ አስቀምጧል። በዚህ መሠረት የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥ...
04/06/2023

መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት አቅጣጫ አስቀምጧል። በዚህ መሠረት የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ ጀምሯል።

በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላት እንደ ምርጫቸውና እንደ ፍላጎታቸው በመከላከያ፣ በፌደራል ፖሊስ ወይም በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ። በዚህ ሐሳብ ላይም ከልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ጋር ከመግባባት ላይ ተደርሷል። ቀደም ብሎም በሁሉም ክልል አመራሮች ጥናት ተደርጎበት፣ በተገኘው ውጤትም ያለምንም ልዩነት ውሳኔው ስምምነት ተደርሶበታል ። ይህ ተግባር እንዲፈፀም መላ ህዝባችንም ሲጠይቅ ቆይቷል። ይሄንን ተከትሎም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

የክልል ልዩ ኃይልን በተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች የማካተት ውሳኔና የተግባር እንቅስቃሴ በጥናት ላይ ተመሥርቶ የሚከናወን ነው። ይህ አካሄድ የኢኮኖሚ ዐቅማችንን በማሰባሰብ የሠራዊታችንን የሥልጠና፣ የትጥቅ እና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ አለው። ይሄንን በመረዳትም በሁሉም ክልሎች ሂደቱ በመግባባትና በውይይት እየተከናወነ ይገኛል።

ሆኖም በአማራ ክልል በሚገኙ የተወሰኑ የልዩ ኃይል ክፍሎች ውስጥ፤ በአንድ በኩል የመልሶ ማደራጀት ሥራውንና ዓላማውን በአግባቡ ባለመረዳት፤ በሌላ በኩል የጥፋት አጀንዳ አራጋቢዎች ሆን ብለው በሚነዙት የሐሰት ወሬ በመጠለፍ ሂደቱን የሚያውኩ ተግባራት ታይተዋል።

ከሚነዙት የሐሰት አጀንዳዎች መካከል፤ የመልሶ ማደራጀቱ መርሐ ግብር በአማራ ክልል ብቻ እየተካሄደ ነው፤ ሕወሐት ትጥቅ ሳይፈታ እንዴት የክልሉ ልዩ ኃይል ትጥቅ ይፈታል የሚሉትና ሌሎችም ይገኙበታል። እነዚህ አጀንዳዎች ሂደቱን ለማደናቀፍ በሚፈልጉ ኃይሎች እየተናፈሱ ይገኛሉ።

የክልል ልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ፕሮግራም በመላ ሀገሪቱ የሚተገበር ነው። ሥራውም በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኝ ነው። ሂደቱንም መንግሥት በጥናት፣ በዕቅድ እና በጥንቃቄ እየመራው ይገኛል። ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ተግባር በሚፈጸምበት ጊዜ።፣ በክልሎች አስተማማኝ ሰላምና ጸጥታን ለማረጋገጥ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ቦታዎች ሥምሪት ወስዷል።
በሌላ በኩል ሕወሐት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ እየተደረገ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። የሕወሐት ትጥቅ የመፍታት ሂደት በተፈረመው ስምምነት መሠረት ያለማወላወል የሚፈጸም እንጂ ከሌላ ሀገራዊ ዕቅድ ጋር የሚቀናጅም የሚጣረስም አይደለም።

የሂደቱ ዋና ዓላማ የትኛውንም ልዩ ኃይል ትጥቅ ማስፈታት አይደለም። ልዩ ኃይሉ ትጥቁን ይዞ እና የተሻለ ዐቅም ተፈጥሮለት በምርጫው መሠረት የክልል ፖሊስን፣ የፌደራል ፖሊስን ወይም የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ማድረግ ነው።

በዚህ ሂደት መካተት የማይፈልግ ማንኛውም የልዩ ኃይል አባል ካለ መብቱ ተጠብቆ ወደ መደበኛ የሲቪል ሕይወት እንዲገባ መንግሥት አስፈላጊውን የማቋቋም ሥራዎች ይሠራል። እንዲቋቋምም ድጋፍ እንደሚያደርግ ያስታውቃል።

የክልል ልዩ ኃይሎችን እንደገና የማደራጀቱ ሥራ መንግሥት ለዘላቂ የሀገር ጥቅምና ደኆንነት የወሰነው ውሳኔ በመሆኑ ኃላፊነቱንም በከፍተኛ ጥንቃቄ ይወጣዋል። ስለዚህ በተለያዩ የጥፋት አጀንዳ አራጋቢዎች ከሚሠራጩ አሳሳች መረጃዎች በመራቅ መላው ሕዝብ እንዲሁም የክልል ልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ለመርሐ ግብሩ ስኬት እንዲረባረቡ መንግሥት ያሳስባል።

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት

መጋቢት 28 /2015 ዓ ም

"የሰማዕታት አደራ፤ የደም ተቋም" በ Mulualem G. Medhin በአራቱም ማዕዘናት ተወርዋሪ ናቸው። የግዳጅ አፈጻጸማቸውን በቅናት ሳይሆን በቅንነት ያስተዋሉ ሁሉ ይመሰክራሉ፦ እጅግ ታጋሽ...
04/06/2023

"የሰማዕታት አደራ፤ የደም ተቋም" በ Mulualem G. Medhin

በአራቱም ማዕዘናት ተወርዋሪ ናቸው። የግዳጅ አፈጻጸማቸውን በቅናት ሳይሆን በቅንነት ያስተዋሉ ሁሉ ይመሰክራሉ፦ እጅግ ታጋሽ ናቸው፤ ተሎ አይሞቁም። በጣም ብርቱ ናቸው፤ በቀላሉ አይሰበሩም። ፈጣን ናቸው፤ ጠላት አሳድደው አይለቁም። ንሥር ናቸው፤ ዒላማቸውን አይስቱም። ካልነኳቸው አይነኩም። በሕዝብና በሀገር ከመጡባቸው ግን ድርድር አያውቁም።

ከጸረ-ሕዝብና ጥቅመኞች ጋር ሰልፍ የላቸውም። ፍትሐዊ ካልሆነ ለመሪያቸውም ቢሆን አይታዘዙ። እኩልነት ቋንቋቸው ነው። ፍትሐዊነት አርማቸው ነው። ከራስ በላይ ለሌሎች መኖር የህይወትና የሙያ መንገዳቸው ነው። ሕዝባዊነት ደግሞ የቆሙለት ዓላማ!

ከክልላቸው አልፎ የሀገረ-መንግሥቱ ዘብ ናቸው።
መውስ እንጅ መስራት የማያውቁት ይቀኑባቸውል።

ስለጦር ብልት አዋቂነታቸው ተመስክሮላቸዋል። ደጀናን ጥሰዋል፤ ግራ ካሶን ቆርጠዋል። ደደቢትን በባሩድ አጥነዋል። በጠላት ሬሳ ላይ ተመላልሰዋል። የጠላትን ምሽግ በቅጽበት ሰብረዋል። የማይሞት ታሪክ ሰርተዋል።

ለጠላት የማይበገሩ የነጻነት ቀንዲሎች መሆናቸውን ወዳጅም ጠላትም ያውቃል።

ውትድርና ደሙ ውስጥ ካለ ሕዝብ መሀል ነውና የወጡት ጀግንነታቸው በወታደራዊ ሥልጠና ብቻ የተገኘ አይደለም፤ ዘመን ተሻጋሪ ነው።

በመታወቂያ መጠሪያቸው የአማራ ልዩ ኃይል
በተግባራቸው የኢትዮጵያ ዋስና ጠበቃ ናቸው።

መውረስ እንጅ መስራት የማያውቁት ተረኞች ስለሚጠሏቸው ሊያፈርሷቸው ቆርጠው ተነስትዋል። ግና፣ የማታ ማታ የሪፐብሊኩ ዘቦች ንሥሮቹ ናቸው‼️

አሜሪካ ወደ አፍሪካ የመንግስት ሥርዓት እንኳን በደህና መጣሽ!🙏"ልጅ ይሮጣል እንጅ አባቱን አይቀድምም።" በነካ እጅሽ ኢራቅን፣ ሶሪያን፣ የመንን፣ ሊቢያን፣ ወዘተ በማፈራረስ ህዝቦችን ሀገር ...
04/04/2023

አሜሪካ ወደ አፍሪካ የመንግስት ሥርዓት እንኳን በደህና መጣሽ!🙏

"ልጅ ይሮጣል እንጅ አባቱን አይቀድምም።"

በነካ እጅሽ ኢራቅን፣ ሶሪያን፣ የመንን፣ ሊቢያን፣ ወዘተ በማፈራረስ ህዝቦችን ሀገር አልባ ያደረጉትን እና የሀገር ሀብት የዘረፉትን ጆርጅ ቡሽ፣ ቢል ክሊንተን፣ ባራክ ኦባማን ለህግ አቅርቢና አስደምሚን።😁

ከዚያም ታሪክሽን እንዲህ እንጽፋለን፤

Once upon a time, US America was a "world leader", a model of "fake democracy", the father of mass destruction, and a legalized looter of poor nations and puppets around the world.

Now, they have officially converted to their true "identity", Africa.

ፍትህ ለዶናልድ ትራምፕ!!😂

ትራምፕ ከእስራት አምልጦ በቀጣዩ ምርጫ እንደምንም ካሸነፈ አሜሪካ ሆይ ወዮልሽ፣ ስደትሽ በክረምት እንዳይሆን በርትተሽ ፀልይ።

Address

Washington D.C., DC

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nigat ንጋት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Nigat ንጋት:

Share