01/31/2026
#ይቻላልን ተጋራሁ።
ለሃይሌ እውቅና ሰጥቼ ቃሉን እንደተጋራሁ ንገሩልኝ።
#በዓለም ዙሪያ ያሉ ወንድሞችን አንድ ሁነው፣በአንድ ልብ ፣ለጋራ ጉዳይ ሊመክሩ፣ በአንተ ሆቴል በአንተ አስተናጋጅነት፣ይቻላል የሚለውን ቃል እንችላለን ብለን መጠቀም ጀምረናል ብላችሁ ንገሩልኝ። እንደማከብረው ልቡ ያውቃል። ቀና እንደሆነ ምስክሩ እኔ ነኝ።
#ዐይናማ የቤተክርስቲያን ልጆች፣ ባለ ብዙ ተሰጥኦ ብዙ መሥራት የሚችሉ፣ ጎራ ለይተው፣አንዳዶቹ በራሳቸው ሌሎች በጓደኞቻቸው ወይም በተከታዮቻቸው ውክልና መንቃቀፍን አዘውትረዋል።
አንዳዶች እንዳይቀርባቸው፣በስምአቸው ሲያፍሩም ፣በተውላጠ ስም የመተቻቸቱን ጎራ ተቀላቅለዋል።
ይህ አካሄድ ዝም ከተባለ ቤተክርስቲያንና ምእመኑን ይጎዳል። ሊቃውንቱንም ያደክማል። ብዙ ሊሰሩ የሚችሉ ወንድሞችን ጊዜ ይሻማል።
ሊቃውንቱም ከማይገባቸው ቦታ ዋሉ። መንቀፍ ቀርቶ መከበር ሲያንስባቸው የሚባሉ ወንድሞች የትችት ዶፍ ወረደባቸው።
ብዙ መሥራት፣በተሰጣቸው ጸጋ ተአምር ይሰራሉ ብለን ያስብናቸውን ተራው አሉቧልታ በላቸው። በዚህ መካክል ጠላት የማይታርቅ የጥላቻ ግድግዳ እየገነባ ሄደ።
ለዘመናት አብረው የኖሩ ወንድሞች፣ ፊት ተዟዟሩ፣ አንዳዶችም በቃላት ተጎድተው የቃላት ቁስለኞች ናቸው።
ጊዜ አይጠብቅም ይፈጥናል። እኛ ግን ተኝተናል። ሀገር በብዙ መከራ ውስጥ ናት። ቤተክርስቲያን ባለቤት አልባ ከመሰለች ቆየች። አዛዥና ታዛዥ ፣መካሪና ተመካሪ፣ አዋቂና ተጠያቂ የመሳሰሉት ቦታቸው ለቀቁ። አንዳንድ ቦታ ወንበር ተቀያየሩ።
እርግጥነው በሶሻልሚዲያው የሚተዳደሩ አሉ።የግድ ትችትና ነቀፋ ውስጥ ሳይገቡ መሥራት ይችሉ ይሆን? ይህንንም አላየነውም። ሶሻልሚዲያው ለብዙ ጉዳዮች ጠቃሚ ቢሆንም ፣በእኛ ወንድሞች በኩል እጅግ ተጠቃሚ የሆነ፣ ያለ አይመስለኝም።
በመነቃቀፋችን ተጠቃሚ የሆኑ ብዙ አካላት እንዳሉ ግን አይካድም። በተለይ ቢተቹ ገበያ የሚያወጡ ወንድሞች መንቀፍ የተለመደ ሁኗል።
በሌላ በኩል፣ ቢሰራ የሚያምርበት፣ቢናገር የሚሆንለት ሰው ባልባሌ ጉዳይ ጊዜውን እንዲያባክን ማድረግ ይቅርታ የማያሰጥ በደል ይሆናል።
ተቆርቋሪ መስለው ፣ለተቸው ወገን ሁነው መልስ የሚሰጡትም፣ሆኑ ቀድሞውኑ ነገሮችን እንዲተቹ የሚያመቻቹ ሁሉ ከህሊና ዳኛ ተጠያቂነት አያመልጡም።
አሁን እንችላለን ብለን የተነሳነው። ማንም ሰው ወንድሙን ነቅፎና አስነቅፎ የውስጥ ደስታ አይሰጠውም
።ከሰጠውም ለጊዜው ነው። እየቆየ ግን ጸጸት ነው።
ከዚህ ጸጸት መዳን እችላለን። መምህራን ነን ።እንኳን ለራሳችን ለሌሎች ተርፎን እናስተምራለን። ይበደሉንን ይቅር እናላለን። ተበድለንም ቢሆን ይቅርታ እንጠይቃለን።
ወንድማችንን የሚያስደስተው ከሆነ፣ካሣም እንከፋለን።ተባብለን አንድ ሁነን።እከሌ ወከሌ ሳንል ተግባብተን ልንተራረም ቆርጠን ተንስተናል እንችላለን። ይህን ሃሳብ ካነሳሁበት ጊዜ ጀምሮ የተረዳሁት፣ እንደጠበኛ ያየናቸው ወንድሞች አንዱ የአንዱ ጥሩነት ያውቃሉ ይመሰክራሉ። ድከመታቸውን ይገነዘባሉ። እንዳልተገነዙትና ፣እንዳልተረዱት ያምኑሉ። በአንዳዶች ንግግር የሚያጣላቸውን አጥቸዋለሁ። አንድ የሚያደርጋቸውን ብዝቶ አግኝቻለሁ። እንደሚዋደዱ ተረድቻለሁ። ጥቃቅን ጉዳዮችን ናቸው አላከበረኝም፣ አልተረዳኝም፣ የመሳሰሉት ናቸው።
መጋራጃው ሲከፈት እንደ ቤተመቅደስ አምረውና ተውበው እንደሚታዩ ተስፋ አለኝ።
ሁሉም ለቤተክርስቲያንና ለሀገር እጅግ አስፈላጊ ናቸው። ታዋቂ ብቻ ሳይሆን አዋቂ ናቸው። ዝም ብለን ልጠቀምባቸው የሚገቡ፣ ሰዎች ናቸው። መላእክት አይደሉም። ሰዋዊ ስህተት አይኖርም ፍጹም ናቸው ብዬ እየመሰከርኩ አይደለም። በጠቅላላ ይዘቱ እንጅ ከብዞቹ ጋር፣ በሀገር ርቀት፣በሌላም ምክንያት ሩቅ ነኝ አንተዋወቅም።
#የፓለቲካ እሳቤዎቻችን የእየግል ናቸው። ፓለቲካው ከመጣንበት ሀገር አያያዙንም እንማራለን። የፈለግነውን ማራመድ እንችላለን። አንድ ቦታ ባንሆን ሁሉም ቦታ ብንኖር እንጠቅማለን። የግድ የኔ ሃሳብ ጠብቅ አንልም። በዚያውስ ላይ የቤተክርስቲያን ልጆች እኮ መናጆ እንጅ በዋናነት በፖለቲካው አይታዩም። የሉም። መቼም እኛ ስም የሰጠነው ሁሉ ፖለቲከኛ አይሆንም።
የእውነት የገቡ ካሉም በእያለንበት በቻሉት ሁሉ፣ቤተክርስቲያንና ሀገርን ላለመጉዳት እጥራለን።
መስሎ ከታየን ደግሞ እንመካከራለን። በወንድሞች እናስመክራለን። ፓለቲካ ባህሉ ስለሆነ ፣በፓለቲካው ዘርፍ ፣ቀን ጎራ ለይተን ተከራክረን ማታ አብርን እናመሻለን። ሻይ ቡናም ስንል በባህላችን እኔ ልክፈል እኔ ልክፈል እንባባላለን።
የፖለቲካው ጨዋታ ሳይገባንም መግባት እንደሌለብን እንማማራለን። ብዞቻችን የምኖረው በሰለጠነው ዓለም ነው።
ከዚህ የምንማረው ብዙ አለ። የሃይምኖት ጉዳይ ከፖለቲካው ብዙ ይርቃል። ሁሉ ነገር እውነት ነው። ሁሉ ነገር መሆንን ይጠይቃል። አክብር ስትል አክብሮ ማሳየት ይጠይቃል።
ተዋደድ ስትል ተዋዶ መኖርን ያስገድዳል። ተፋቀሩ ስትል እግዚአብሔር ፍቅር መሆኑን ትስብካለህ። ታዲያ አንተ የት ትሄዳለህ። ?
ተፋቅረህ አሳየን የሚል ጥያቄ በውስጥም በውጭም ይፈጠራል።
ወንድሞች ሁሉን እንችላለን። ብንከባበር የምታርፈውን እንጅ የምናጎደለው ምንም የለም።
ብንስማማ ካለን የሚጎድልብን የለም። ተስማምተን እንሞክረውና እኔ ልቀጣ።
#የመጀመሪያ ሥራው በጣም የታወቁትን በአውድምሕረት ቁመው የሚያስተምሩትንና ሲያስተምሩ የነበሩትን ያስቀድማል። እነዚህ አንጋፋዎቹ ከመከሩና በደንብ ከተስማሙበት በኋላ በእየአህጉሩ በእነሱ መሪነት የቤተክርስቲያን ልጆች ሁነው በሚዲያ ያሉ ፣አነሰም በዛም የእየራሳቸው አስተዋጾ የሚያደርጉትን አህጉራዊ፣ አገራዊና ፣ከተማዊ፣ ምክክሮች ይደረጋሉ። ሥራው ሰፊ ነው።
የሚጀምረው ከምንጩ ነው።
አንጋፋዎቹ ወረድ ብለው በትህትና ወንድሜ በድየህ ከሆነ ይቅር በለኝ ብለው፣ ትህትና ከልብ በመሆን የሚያስተምሩበት፣ ማስመሰልና ኢሉታ ተወግደው እውነት የሆነ ወንድምነት የሚታይበት ሃሳብ አስተናል።
ወንድሞች ይህን ማድረግ እንችላለን። ለኅኃይሌም ንግሩት፣ይቻላልን መከባበርና አንዳችን ለአንዳችን አቅምና ክብር መሆናችንን ለማሳየት እንችላለን።
አንድ ቀን ጊዜው ሲደርስ፣ እግዚአብሔር ሲፈቅድ በአንተ ሆቴል ተሰባስበን፣ አንተ አስተናጋጅ ልትሆን ይቻላል። ብሏል በሉኝ።
የዘመናት ውብ ቃል ሁኖ ለድል ያበቃህን ቃል/ መፈክርን/ በእሱ ቤት መጨረስ ስለሚገባ ይህም ይቻላል። አወ ተራርሞ መከባበር እንችላለን። ከእንግዲህ በሶሻልሚዲያ መካሰሱን በሞጋገስ ተክተን ቤተክርስቲያንና ሀገርን ልናገለግል ቃል መግባት እንችላለን። እንችላለን።