Ethiopia African

Ethiopia African Property Management Arsenal Fans

02/02/2026
01/31/2026

#ይቻላልን ተጋራሁ።
ለሃይሌ እውቅና ሰጥቼ ቃሉን እንደተጋራሁ ንገሩልኝ።

#በዓለም ዙሪያ ያሉ ወንድሞችን አንድ ሁነው፣በአንድ ልብ ፣ለጋራ ጉዳይ ሊመክሩ፣ በአንተ ሆቴል በአንተ አስተናጋጅነት፣ይቻላል የሚለውን ቃል እንችላለን ብለን መጠቀም ጀምረናል ብላችሁ ንገሩልኝ። እንደማከብረው ልቡ ያውቃል። ቀና እንደሆነ ምስክሩ እኔ ነኝ።

#ዐይናማ የቤተክርስቲያን ልጆች፣ ባለ ብዙ ተሰጥኦ ብዙ መሥራት የሚችሉ፣ ጎራ ለይተው፣አንዳዶቹ በራሳቸው ሌሎች በጓደኞቻቸው ወይም በተከታዮቻቸው ውክልና መንቃቀፍን አዘውትረዋል።

አንዳዶች እንዳይቀርባቸው፣በስምአቸው ሲያፍሩም ፣በተውላጠ ስም የመተቻቸቱን ጎራ ተቀላቅለዋል።

ይህ አካሄድ ዝም ከተባለ ቤተክርስቲያንና ምእመኑን ይጎዳል። ሊቃውንቱንም ያደክማል። ብዙ ሊሰሩ የሚችሉ ወንድሞችን ጊዜ ይሻማል።

ሊቃውንቱም ከማይገባቸው ቦታ ዋሉ። መንቀፍ ቀርቶ መከበር ሲያንስባቸው የሚባሉ ወንድሞች የትችት ዶፍ ወረደባቸው።

ብዙ መሥራት፣በተሰጣቸው ጸጋ ተአምር ይሰራሉ ብለን ያስብናቸውን ተራው አሉቧልታ በላቸው። በዚህ መካክል ጠላት የማይታርቅ የጥላቻ ግድግዳ እየገነባ ሄደ።
ለዘመናት አብረው የኖሩ ወንድሞች፣ ፊት ተዟዟሩ፣ አንዳዶችም በቃላት ተጎድተው የቃላት ቁስለኞች ናቸው።

ጊዜ አይጠብቅም ይፈጥናል። እኛ ግን ተኝተናል። ሀገር በብዙ መከራ ውስጥ ናት። ቤተክርስቲያን ባለቤት አልባ ከመሰለች ቆየች። አዛዥና ታዛዥ ፣መካሪና ተመካሪ፣ አዋቂና ተጠያቂ የመሳሰሉት ቦታቸው ለቀቁ። አንዳንድ ቦታ ወንበር ተቀያየሩ።

እርግጥነው በሶሻልሚዲያው የሚተዳደሩ አሉ።የግድ ትችትና ነቀፋ ውስጥ ሳይገቡ መሥራት ይችሉ ይሆን? ይህንንም አላየነውም። ሶሻልሚዲያው ለብዙ ጉዳዮች ጠቃሚ ቢሆንም ፣በእኛ ወንድሞች በኩል እጅግ ተጠቃሚ የሆነ፣ ያለ አይመስለኝም።

በመነቃቀፋችን ተጠቃሚ የሆኑ ብዙ አካላት እንዳሉ ግን አይካድም። በተለይ ቢተቹ ገበያ የሚያወጡ ወንድሞች መንቀፍ የተለመደ ሁኗል።

በሌላ በኩል፣ ቢሰራ የሚያምርበት፣ቢናገር የሚሆንለት ሰው ባልባሌ ጉዳይ ጊዜውን እንዲያባክን ማድረግ ይቅርታ የማያሰጥ በደል ይሆናል።

ተቆርቋሪ መስለው ፣ለተቸው ወገን ሁነው መልስ የሚሰጡትም፣ሆኑ ቀድሞውኑ ነገሮችን እንዲተቹ የሚያመቻቹ ሁሉ ከህሊና ዳኛ ተጠያቂነት አያመልጡም።

አሁን እንችላለን ብለን የተነሳነው። ማንም ሰው ወንድሙን ነቅፎና አስነቅፎ የውስጥ ደስታ አይሰጠውም
።ከሰጠውም ለጊዜው ነው። እየቆየ ግን ጸጸት ነው።

ከዚህ ጸጸት መዳን እችላለን። መምህራን ነን ።እንኳን ለራሳችን ለሌሎች ተርፎን እናስተምራለን። ይበደሉንን ይቅር እናላለን። ተበድለንም ቢሆን ይቅርታ እንጠይቃለን።

ወንድማችንን የሚያስደስተው ከሆነ፣ካሣም እንከፋለን።ተባብለን አንድ ሁነን።እከሌ ወከሌ ሳንል ተግባብተን ልንተራረም ቆርጠን ተንስተናል እንችላለን። ይህን ሃሳብ ካነሳሁበት ጊዜ ጀምሮ የተረዳሁት፣ እንደጠበኛ ያየናቸው ወንድሞች አንዱ የአንዱ ጥሩነት ያውቃሉ ይመሰክራሉ። ድከመታቸውን ይገነዘባሉ። እንዳልተገነዙትና ፣እንዳልተረዱት ያምኑሉ። በአንዳዶች ንግግር የሚያጣላቸውን አጥቸዋለሁ። አንድ የሚያደርጋቸውን ብዝቶ አግኝቻለሁ። እንደሚዋደዱ ተረድቻለሁ። ጥቃቅን ጉዳዮችን ናቸው አላከበረኝም፣ አልተረዳኝም፣ የመሳሰሉት ናቸው።
መጋራጃው ሲከፈት እንደ ቤተመቅደስ አምረውና ተውበው እንደሚታዩ ተስፋ አለኝ።
ሁሉም ለቤተክርስቲያንና ለሀገር እጅግ አስፈላጊ ናቸው። ታዋቂ ብቻ ሳይሆን አዋቂ ናቸው። ዝም ብለን ልጠቀምባቸው የሚገቡ፣ ሰዎች ናቸው። መላእክት አይደሉም። ሰዋዊ ስህተት አይኖርም ፍጹም ናቸው ብዬ እየመሰከርኩ አይደለም። በጠቅላላ ይዘቱ እንጅ ከብዞቹ ጋር፣ በሀገር ርቀት፣በሌላም ምክንያት ሩቅ ነኝ አንተዋወቅም።

#የፓለቲካ እሳቤዎቻችን የእየግል ናቸው። ፓለቲካው ከመጣንበት ሀገር አያያዙንም እንማራለን። የፈለግነውን ማራመድ እንችላለን። አንድ ቦታ ባንሆን ሁሉም ቦታ ብንኖር እንጠቅማለን። የግድ የኔ ሃሳብ ጠብቅ አንልም። በዚያውስ ላይ የቤተክርስቲያን ልጆች እኮ መናጆ እንጅ በዋናነት በፖለቲካው አይታዩም። የሉም። መቼም እኛ ስም የሰጠነው ሁሉ ፖለቲከኛ አይሆንም።

የእውነት የገቡ ካሉም በእያለንበት በቻሉት ሁሉ፣ቤተክርስቲያንና ሀገርን ላለመጉዳት እጥራለን።

መስሎ ከታየን ደግሞ እንመካከራለን። በወንድሞች እናስመክራለን። ፓለቲካ ባህሉ ስለሆነ ፣በፓለቲካው ዘርፍ ፣ቀን ጎራ ለይተን ተከራክረን ማታ አብርን እናመሻለን። ሻይ ቡናም ስንል በባህላችን እኔ ልክፈል እኔ ልክፈል እንባባላለን።

የፖለቲካው ጨዋታ ሳይገባንም መግባት እንደሌለብን እንማማራለን። ብዞቻችን የምኖረው በሰለጠነው ዓለም ነው።

ከዚህ የምንማረው ብዙ አለ። የሃይምኖት ጉዳይ ከፖለቲካው ብዙ ይርቃል። ሁሉ ነገር እውነት ነው። ሁሉ ነገር መሆንን ይጠይቃል። አክብር ስትል አክብሮ ማሳየት ይጠይቃል።

ተዋደድ ስትል ተዋዶ መኖርን ያስገድዳል። ተፋቀሩ ስትል እግዚአብሔር ፍቅር መሆኑን ትስብካለህ። ታዲያ አንተ የት ትሄዳለህ። ?

ተፋቅረህ አሳየን የሚል ጥያቄ በውስጥም በውጭም ይፈጠራል።

ወንድሞች ሁሉን እንችላለን። ብንከባበር የምታርፈውን እንጅ የምናጎደለው ምንም የለም።

ብንስማማ ካለን የሚጎድልብን የለም። ተስማምተን እንሞክረውና እኔ ልቀጣ።

#የመጀመሪያ ሥራው በጣም የታወቁትን በአውድምሕረት ቁመው የሚያስተምሩትንና ሲያስተምሩ የነበሩትን ያስቀድማል። እነዚህ አንጋፋዎቹ ከመከሩና በደንብ ከተስማሙበት በኋላ በእየአህጉሩ በእነሱ መሪነት የቤተክርስቲያን ልጆች ሁነው በሚዲያ ያሉ ፣አነሰም በዛም የእየራሳቸው አስተዋጾ የሚያደርጉትን አህጉራዊ፣ አገራዊና ፣ከተማዊ፣ ምክክሮች ይደረጋሉ። ሥራው ሰፊ ነው።

የሚጀምረው ከምንጩ ነው።
አንጋፋዎቹ ወረድ ብለው በትህትና ወንድሜ በድየህ ከሆነ ይቅር በለኝ ብለው፣ ትህትና ከልብ በመሆን የሚያስተምሩበት፣ ማስመሰልና ኢሉታ ተወግደው እውነት የሆነ ወንድምነት የሚታይበት ሃሳብ አስተናል።

ወንድሞች ይህን ማድረግ እንችላለን። ለኅኃይሌም ንግሩት፣ይቻላልን መከባበርና አንዳችን ለአንዳችን አቅምና ክብር መሆናችንን ለማሳየት እንችላለን።

አንድ ቀን ጊዜው ሲደርስ፣ እግዚአብሔር ሲፈቅድ በአንተ ሆቴል ተሰባስበን፣ አንተ አስተናጋጅ ልትሆን ይቻላል። ብሏል በሉኝ።

የዘመናት ውብ ቃል ሁኖ ለድል ያበቃህን ቃል/ መፈክርን/ በእሱ ቤት መጨረስ ስለሚገባ ይህም ይቻላል። አወ ተራርሞ መከባበር እንችላለን። ከእንግዲህ በሶሻልሚዲያ መካሰሱን በሞጋገስ ተክተን ቤተክርስቲያንና ሀገርን ልናገለግል ቃል መግባት እንችላለን። እንችላለን።

01/30/2026

#መነሻችን ጥሩ ከሆነ መድረሻችን ቅርብ ነው።

#ብታደርጉት የምታተርፉበት፣ብትኖሩበት የምትደሰቱበት መሆኑ ቢታወቅም፣ ሃሳቡ ሲነሳ በፍጹም ቅንነትና ወንድምነት በፊት ለፊትም፣በጓዳም መጥታችሁ አለን ያላችሁ ወንድሞች ሁሉ፣ እግዚአብሔር በሁለመናችሁ አለሁ ይበላችሁ!!

#ምንም እንኳን ሥራው የጋራ ቢሆንም አስነሽ ፣አነሳሽ ማስፈለጉ ግድ ነበር። ከብዙ ወድሞች ያልጠበከት ብዙ ጥሩ ነገር አግኝቻለሁ።
ሩቅ የሚመስሉ፣ሃሳቡን በቀላሉ አይቀባሉም የተባሉት ከማንም ቀድመው በፍጹም ቅንነት አዎታዊ መልስ ሰጥተዋል።

መነሻዩ ባለፈው ሳምንት የተከናወነ አንድ በጎ ነገር ነበር። በጎ ሠርቶ መደሰትና ማስደሰት እያለ፣መካሰስን ምን አመጣው? ለምን አንመካከርም፣ አንዳንድ ወንድሞችን ቀርብን ፣ ብንረዳቸው ብናግዛቸው ከማንም በላይ ይጠቁሙናል። ከሚል ቅንነት የመነጨ አስነሽ ሃሳብ ነው።

ልሞክረው በሚል ቅን እሳቤ ጻፉኩት። ቀድሞ የማውቃቸው ወንድሞች ብቻ ሳይሆኑ የማላውቃቸው ፈጣን ምላሽ ሰጡ።

በዚህም ደስ አለኝ። አንድ ቀን በዝርዝር የማመሰግናቸው ወንድሞች እንዳሉ ሁነው አሁን ሃሳቡ የብዞቻችን ሁኗል።

በተለያየ መንገድ ያላግኘኋችሁ፣የጻፍኩላችሁን ያላያችሁ፣ አድራሻ ኑሮኝ ያልጻፍኩላችሁ ትኖራላችሁ። ተጀመረ እንጅ ሥራው ብዙ ነው።

የጊዜውን መረዳቴን እየጻፍኩ ያለሁት። ቤተክርስቲያን ብዙ ውብ ልጆች አሏት። የሚያስተባብራቸውና የሚያቀራርባቸው ጠፍቶ እንጅ ሁሉም ጥሩ ናቸው።

ባየሁትም በደረስኩት ልመስክር የምችለው ይህን ብቻ ነው።

ያለንበት ዓለም ፈጣንና ተለዋዋጭ ነው። እንኳን አደባባይ ላይ ወጥተን ፣ እንዲሁም የሥራችን ባሕሪይ የተገለጠ ነው።

ስህተቶች በየትኛውም አንግል ይፈጠራሉ። ለጥሩ ያሉት ለመጥፎ የሚሆንበት ጊዜ አለ። #ሰዎችነን እንሳሳታለን። የምንሳሳት በመሆኑ ነው። ምሥጢረ ንስሓ የሚል ቀኖና የተሰራው፣ የበደለው እንዳልበደለ እንዲሆን፣ ጥፋተኛው እንደ በጎ አድራጊ የሚታይበት ዘመን እንዲመጣ፣ ባለፈው በመጥፎ ጊዜ ተጸጽቶ አዲስ የመሆንን ያህል የደስታ ምንጭ የለም። የሰማይ መላእክት ሳይቀሩ የሚደሰቱበት ነው። ንስሓ ዘማዊዩን ድንግል ያደርጋል ተብሎ የለ?

ወንድሞች እንደቀድሞው ተከባብረን ፣ተመካክረን፣ተነፋፍቀን መኖርን እንችላለን። ዓለም ሰፊናት የምንኖረው፣በተሰጠኝ ጸጋ፣ሰው ስንሆን እንድኖረው በተወሰነው እድል ወጥተን ወርደን ነው።

የማንን እንጀራ ማን ይበላል?። የማንን ሥራ. ማን ይወስዳል?። ለእኔ የተሰጠው የኔ ነው። የተወሰነው ከሰማይ ነው። ይህን እናምናለን ታዲያ በምኑ ነው የምንጋጨው? እግዚአብሔር ፍቅር ነው። ለእግዚአብሔር ብሎ ጠብ የለም።

ስለዚህ የሚያምርብን ፍቅር እንደሆነ ለቀባሪው እንደማርዳት ይሆናል።

የመጣሁት ሁላችሁንም ለማመስገን ነው።ሁላችሁንም አመሰግናለሁ እግዚአብሔር በክብር ያኑርልኝ።
#የሚጠብቀን ሥራ ብዙ ነው። በጸሎትና በሃሳብ ጉዟችንን ደግፉ። እንደባለቤት ሁናችሁ ምሩ። ለሁላችሁም እንደ አስፈላጊነታችሁ ጥሪ እናቀርባለን። በእየሀገሩም ያሉ መምህራንም በሃሳብ የተሻለውን ሲጠቁሙን ዓለም አቀፍ የመምህራን መተራሪሚያ ሃሳቦችን አናፈልቃለን። በአደባባይ የምእመናን መሰናከያ ከእንግዲህ መሆን የለብንም። ሲሆን ሲሆን ለግላችንም ቢሆን ከኃጢአት ብንጠበቅ የተሻለ የሌለው ምርጫ ነው። ከሆነም የአንዱ ውድቀት ለእኛ ምን ያደርግልናል?። ለጀሮችን ጤንነት ጥሩ መስማት ነው።፣ለዐይናችንም ውበት ጥሩ ማየት ነው።፣ ለህሊናችን ሠላም ጥሩ መናገር ነው። ክፉ ነገርን የምንረቀው ለራሳችን ነው። ክፉ ነገር ከቤታችን አይውጣ ብለን የተማማልን የመስል አንድ ነገር ጋብ ሲል ሌላው እየተወሳ መቁስለን የለብንም። ስመካከር ሁሉም ይቀየራል።
ቤተክርስቲያንን የሚጎዳ ሲሆን ተመካክረን ማረም፣ ሰውየውም እንዳይጠፋ ሌሎችም እንዳይሰናከሉ ማድረግ እንችላለን።

ቤተክርስቲያን እንደምታውቋት ያጠፋን የምትገስጽበት ብዙ መንገድ አለ። ከቀደመው ከአባቶች ጥበብ እንወርሳለን። ከተመካከረን ሁሉ አለን።

በስማ በለው ባልዋሉበት በሌሉበት የሚወቀሱ ወንድሞች ያዝኑብናል ።ቢያዙ ያደርሳሉ።

#ይህንም ማስተካከል ሃላፊነት አለብን።ከሁሉም በላይ ብዙ የሚጠቅሙ ፣ ልጠቀምባቸው የሚችሉ ወንድሞች ባልሆነ አጀንዳ ጊዜያቸውን እንዲያባክኑ ያደርግልናል። ለሚመጣው ይጠብቀን። ለአለፈው ይቅርበለን ብለን ተነስተናል እግዚአብሔርን ይርዳን።
እንደምታዩት መሠረቱ ጥሩ ይመስላል።የሚመለከታችሁ አሁን በውስጥ ጻፉሉኝ። ላላዩት ሼር አድርጋችሁ ወይም ሃሳቡን በራሳችሁ አገላለጽ ወስዳችሁ አጋሩ።
#ማሳሰቢያ
ፎቶ ከጽሑፍ ጋር የተያያዘው በአጻራዊነት እንጅ፣ በአስረጅነት አይደለም። እስከመጨረሻው የማንበብ ልምድ ከሌለን እንዲሁ ይሆናል ።

‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት...
01/23/2026

‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡
መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት።

ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት፡፡

ወዲያው ወታደሮቸ በሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው፡፡
ይህ እንደሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ።

ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት ‹‹በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል›› አለኝ፡፡

‹‹እንዴት?›› ብለው ‹‹አላየህም ሲያጨበጭብ?›› አለኝ፡፡ ‹‹ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል›› አልኩት፡፡

‹‹እንዴት?›› ቢለኝ እጄን አጨብጭቤ አሳየሁት፡፡"
አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ በቦታው ሆነው የተከታተሉት ሙሴ ፓይላክን የተባሉ ግለሰብ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ለጳውሎስ ኞኞ ከነገሩት የተወሰደ፡፡

ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ/ም

Yared Shumete እንዳስታወሰን

01/23/2026

#እኔና መዝሙር የተዋወቅነው

መዝሙርን ያውኩት1985 ክርስቶስ ሠምራ ለመሳለም ሂጄ ነው። በወቅቱ ዝናብ ነበር። ከአንድ የመቃብር ድንጋይ ቤት ጥግ እየዘመሩ ያደሩ የከተማ ልጆች ነበሩ። ሴቶችም አሉበት። እኔም በመገረም ስሰማቸው አደርኩ።

#ከሃያ ሁለቱ አርእስተ ድጓ አንዱ የሆነው መዝሙር ፣በእየሳምንቱ የእሁድ ስብሐተ እግዚአብሔር እንዳለ እንጅ ስመ ሞክሼውን መዝሙር መኖሩን አላውቅም ነበር።

#በቅርቡ ባደረኩት ማጣራት ይህ ከተማ ቀመሱ መዝሙር ገጠር እንዳልገባ ነው። ቆየት ብዬ ሳጠና ወደ ሀገራችን የገባው 1950 መጀመሪያ ወደ ውጭ ለትምህርት ሂደው የተመለሱ፣ ከሌሎች አብያተክርስቲያናት የወረሱት በጎ ባህል እንደሆነ ገባኝ።

በዚህ በኩል ሊቀ ሥልጣናት ሀብተማርያም ወርቅነህ፣የኋላው. አቡነ መልከጼዴቅ ሊመሰገኑ በስማቸውም የሆነ ነገር ማስታወሻ ሊቀመጥ ይገባል። ቅድስት ሥላሴ ሴት አስቀደሱበት ተብሎ በመኳንቱ በተደጋጋሚ ተከሰውበታል። ሊቃውንቱ ሃይማኖታችን አረከሱት ብለው ወቅሰዋቸዋል።

ሴቶች ወጣቶች እንዲዘምሩ ከፍተኛ ድጋፍ ሰጥተዋል። የመዝሙር ስልቱ ብቻ ሳይሆን መዘመሪያው ፒያኖ ከአውሮፓ አስገብተው ነበር። ዛሬም ቅድስት ሥላሴ ውስጥ አለ። እነመምህር እንቆባሕሪይ ፣እነኪነጥበብ ዘምረውበታል።

ምንም እንኳን ኋላ ጠብ ሲመጣ፣ በፒያኖውን ነጥለው ወቀሳ ቢያስከትሉም፣ ተጠቅመውበታል።
መዝሙር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ አስቆጥሯል። በገጠሩ የሀገራችን ክፍል ግን አይታወቅም። ስሪቱ ከሰንበት ትምህርት ቤት ጋር ስለሆነ፣ከተማና ከተማ ዳር ያለፈ የለም።

#ታዲያ የሰሞኑ ጫጫታ ለምን በረከተ። በጎደር ጥምቀትስ ለምን ይህን ያህል ልዩነት ሆነ የሚል ጥያቄ መቅረቡ አይቀርም።

#የመጀመሪያው ሶሻልሚዲያው አጀንዳ ይፈልጋል። ሌላው ተቧድኖ ቢነቃቀፍ ደስ የሚለው ወጣት አለ። ጎንደር ጥምቀት፣ ታቦት ወርዶ ሊቃውንቱ ማሕሌት ሲቆም ሕዝቡ ሲዘፍን ያድራል። በድርሻው የበዓሉን ድባብ ይጋራል።ገጠር ቀመሱ ይህን በድንብ ያውቃል ። ጎንደር ከተማም እየሰፋ መጥቶ ሁኖ ይሆናል እንጅ ከአዲስ አበባ እየሄድኩ በማከብርበት ጊዜም ፒያሳ ላይ ድል ያለ ዘፈን ነበር። ዘፋኞችም ተመርጠው አደባባይ ላይ ሲያወርዱት ነበር። ይህ ማታ ነው። ቀን ታቦቱን ሲያገባ ሆ የሚለው ወጣት የሚዘፍነው ህዝብ ባህሉ ነው ።
አሁን አሁን የዘማሪው ወጣት ቁጥርም ጨምሯል። እድገቱን ሁኔታውን መረዳት እንጅ ፣ሃይማኖታዊ ዳራ ብቻ ሰጥቶ መነቃቀፍ አግባብ አይሆንም። ጥምቀት፣የሀሉም ህዝብ የአደባባይ በዓል እንጅ ፣ትውፊት አልባ፣ ባህል የማያውቅ አድርጎ መገመቱ ልክ አይመስልም።

በጭራሽ የሀገራችን ባህልም የማያውቅም፣እሱ ከሚያውቀው ውጭ ያለ የማይመስለው አለ። በስሜት የሚሄድ፣በእልህ የሚናደድ የተደናገረ ትውልድ አለን።

አንዳዶች በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፈን የተወገዘ ነው ብለው ለመከራከር የሚደክሙ. አሉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፈን፣ ተመስግኗልም ተተችቷልም። የዳዊት በታቦቱ ፊት መዝፈን ክብር ሲያሰጥ፣በቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት የገላትያ ዘፈን ተወግዟል። ዘፈን እንደተጠቀሰበት አውድ እንጅ፣በቃሉ የተሰጠው ብያኔ የለም።

ይጣላል ቢሉ አይጣላም። ዘፈን እንደየባህሉ ይለያያል። መጽሐፍቅዱስን መጥቀስ ያለብን የተጻፈበትን ባህል አውቆ ነው።

የእኛ ትርጓሜ ወይም አንድምታ ፣ሲያብራራ፣እንደ ቋራ፣እንደ ቆራጣ፣እንደ ፎገራ እያለ የሚጠቅሰው የእነሱ ባህል ይህን ይመስላል ለማለት ነው። የተጻፈበትን መሠረታዊ ባህል እያስረዳ ወይም ዋቢ እየጠቀሰ ነው። የእስራኤል ባህል ብዙ ነገሩ በሰሜኑ ሀገራችን ክፍል ይመስለዋል። ቃሉ በተጠቀሰበት ክፍል መስሉን ትርጓሜ ያብራራዋል።

ባህል የሌለው ጽሑፍ፣ መሠረቱ ባህል ያልሆነ ሃይምኖት የለም።
አንድን ሃይምኖት ለማወቅ፣ መሠረቱን ፣ባህሉንና ደግማውን ቀኖናውንና ትውፊት ማወቅ ግድ ይላል ። ለመረዳት በፈለገን ቁጥር እውቀት ይጨምራል። ባወቅን ቁጥር አለማወቅህን ከማወቅ ውጭ ሌላውን የሚያስተች ትምህርት ቤተክርስቲያን ውስጥ የለም። ቅድስናም እየበቃህ ስትሄድ የሰው ታላቅነት ያስረዳሃል እንጅ ተሳዳቢ አያደርግም።

ሃይማኖቱን የማያውቁ ሃይማኖተኞች በዝተዋል። ምክንያት ፈልገው ውዝግብ የሚፈጥሩም አሉ። ከእነዚህ ሰዎች መራቅ ይገባል። #ተነጋገርን፣ከተማማርን ስህተትን የመሰለንን ሁሉ ማረም መረዳዳት እችላለን። ያልጋባው እሱ ያወቀው ብቻ እውነት መስሎት የሚጣላ፣ለሃይማኖቱ ብሎ የሚናድድ አይጠፋም።

#ለሁሉም ከመተቸትህ በፊት፣ ስለጉዳዩ በደንብ እወቅ፣ ከመተቸትህ በፊት ተማር። እርግጠኛ ሁኜ የምንገርህ፣ከተማርክ ነቃፊ አትሆንም ። በየትኛውም መንገድ ያልደረስክበት እንዳለ እንጅ የምትነቅፈው አንተ ብቻ የምታውቀውም እውቀት የለም።

#ስለምትነቅፈው ብቻ ሳይሆን ስለምደግፈው በደንብ ማወቅ አለብህ። እርግጠኛ ይህን ካነበብክ በኋላ። በዘፈንና በዘፋኝ ላይ የምታዘወትረው ስድብ ትገታዋለህ።

ይህ ብቻ አይደለም ። አስፍተህ ትመረምራለህ። የት መጣውን ታውቃለህ። ያንጊዜ ስህተት እንኳን ቢኖረው መነሻው ከገባህ ለማረም አትቸገርም። የኔ ገጽ ደበኛ ለመሆን እንኳን የአንባቢና የኮሜት ሰጭ ሕግ አለ። ክብር ያላቸውን ቃላት ተጥቅሞ ማረም እንጅ ተራ ቋንቋ የሚጠቀም ሲገኝ ፣ወደ መሰልህ ሂድ ተብሎ ይሰናበታል። ይህም ባህል ነው። አክብረህ አንብብ ወዳጄ።
#ሊቀ ኃይላት ፍሬሰው ደምስ

01/21/2026

#የተወለድኩባት። ገጠር ከከተማ የራቀች ፣አንዲት ጥንታዊ መንደር ናት።
እስካሁንም ድረስ የመኪና ድምጽ አይሰማባትም።
የመብራት ብርሃን የላትም።

ውሃ በዘመናዊ እግሩ አይሄድባትም። በተፈጥሮ ከዚያው ከምንጩ ነው የሚቀዳው።

#ብዙው ሰው አሁንም ድረስ ከዘመናዊ ትምህርት ጋር አይተዋወቅም። ተምሯል ከተባለ የቄስ ትምህርት ዳዊት ደጋሚ ነው።
የልጅነት ዋና ሥራችን ከብት መጠበቅ ነበር።
መሠረተ ትምህርት የሚባል መጥቶ ከፊደል ጋር ሲያስተዋውቀኝ። መምህራኑ ወደዱኝ።ለመደበኛ ትምህርት ሊወስዱኝ ሲሉ አባቴ ግን ዘመን አመጣሽ ትምህርት መልመድ የለበትም ብሎ ለአበልጁ በአደራ የቄስ ትምህርት እንዲያስተምሩን ሰጠኝ።

#የጉዞዬ አቅጣጫ ተቀየረ። የቆሎ ተማሪ ሆንኩ። ትንሽ ከመሆኔ የተነሳ ስሜም ፍሬው ተባለ።

ያ ነቢይ የመሰለው ባለሀገሩ ዘመዳችን ያወጣልኝ። ስሜን ከግብሬ የሚገልጸው ስም ተለወጠ።
የቆሎ ትምህርት ቤት ባህሉ እንዳይቀር ፣ላለመታወቅ ስምንና የመጡበትን አካባቢ መደበቅ፣ሕግን ተከተልኩ። ድሮ ጀምሮ የወጡ ደንቦች አከብራለሁ።

#እንደሌሎች ብዙ ባልቀያይርም። የልጅነት ስሜ ተለወጠ። ቀጣዩ የፊደል ቅርጽ፣የማጠርና መርዘም እንጅ ብዙ አልተለዋወጠም።

ወደ ከተማ ለመግባትም ልጅነቴ ረድቶኛል። ልጅ ባየው ነገር ይሳባል። ችግሩን አርቆ አያስብም። ከፊት ለፊት የሚገጥመኝ ችግር ሳላስብ ፣በድፍረት አዲስ አበባ ገብቼ የከተማ ሰው ሆንኩ።

#ያለምንም እርዳታ እራሴን ፈልጌ አገኘሁ። ከክርስቶስ ደም ቀጥሎ የእኔም ደም መሠረት ሁኖታል የምለው የሴምሲው ሚካኤል ነው። በጥር ተመሥርቶ በየካቲት ገልጋዩ ሆኜ ፣ በሳጠራ ግድግዳ፣በቆርቆሮ በር ፣በአትሮኑስ መንበር ቤተመቅደሱና ቤተልሄየሙ አንድ ሁኖ አገልግያለሁ ።

በእኔ ደም የምለው ከገጠር እንደመጣሁ። በፍጹም ፈራሔ እግዚአብሔር እውነትን ይዤ የታገልኩበት ቦታ ነው። የታቦት ገንዘብ ይቀስፋል። አይነካም ብዬ መሟገቴን ሳስበው አሁን ላይ ሞኝ እንደሆኑ ይሰማኛል። በእኔ አቅም የሚቆም ሌብነት አልነበረም።

ሰዎቹ ከተማ የቆዩ ልምድ ያላቸው። ቀኝ አሳይተው በግራ የሚነጥቁ ፈጣኖች ነበሩ። ዛሬ ያዚያን ጊዜዎቹ ለታሪክ ነጋሪነት እንኳን መኖራቸውን እጠራጠራለሁ። ተበታትነው። አዲሶች ቦታውን ይዘውታል።

የገጠር ልጅ መሆን ለእውነት የመቅረብ ያህል ስሜት አለው። ከተማና ከተማ ዳር የተወለደ ማስመሰልም፣መምሰል ይችላል። ብዙ አይጋፈጥም።

ገጠር በመወለዴ እልፍ ጥቅሞች ቢኖሩትም፣ አንዳንድ ጊዜ ቀንቶ ለማይቀናው፣ጊዜ ያባከንኩበት ያስቆጨኛል።

#ከዚያች ትንሽ ገጠር ተነስቼ አውሮፓን ለማየት፣መከለኛውም ምሥራቅን ለመጎብኘት ብዙ ጊዜ አልፈጀብኝም።

ወደ አሜሪካም ያለ ብዙ ድካም መጣሁ። አሁን ዓለምን ከምትዘውረው ሀገር ላይ ሁኜ፣ የዓለምን የወርቅ ኤዩቪልዩ የሚባለው የእድሜ ቁጥር ውስጥ መግባቴን በይፋ አወጅኩ። ተፈጥሮም እንዲህ እንዲሆን አስገደደኝ።

ለእግዚአብሔር የሚሳነው የለም። ከትቢያ አንስቶ ከዚህ አደረሰኝ። ከእረኝነት አውጥቶ ዓለምን አዞረኝ። ማንም ሳይኖረኝ። በታሪክ እንዲህ እረዳሁት የሚል ባለታሪክ ከጎኔ ሳያስቀምጥ፣ ባለቤቱ መድኃኔዓለም መንገድ ሆነኝ።

እልፍ አእላፍ ወዳጆችን በዓለም ዙሪያ አፍርቻለሁ። ከእናቴ ማህጸን ስወጣ ራቁቴን ነበር።

አሁን የልብሴ ብዛት ቆጥሬው አላውቅም። ሳድግ በአንድ ተጠጀባብ። በዓመት አንድ ጊዜ ያውም የጥምቀት የተገዛልኝ ነበር ልብሴ ። አሁን ገዝቼ ያለብሰኩት በመስቀያው ተደርድሯል።

የሚያኖር እግዚአብሔር ትላንት በቆሎ ተምህርት ቤት ሕግ መሠረት ኮቾሮ አጠራቅሜ ከውሻ ጋር ታግዬ የእለት ጉረሴን እሞላ ነበር።

ዛሬ ተጠርቼ አማርጬ ፣ተለምኜ/ተገልግዬ/ነው የምበላው ስለበላሁላቸው ደስ የሚላቸው ብዙ ወዳጆች እግዚአብሔር ሰጠኝ። ዛሬ ጎደሎ የሚመስለው ሕይዎቴ ሁሉ ሙሉ እየሆነ ነው።

ትላንት ያልነበረኝ ዛሬ አለኝ። የእንጨት ጎጆ ለመሥራት ልጅ በመሆኔ እቸገር ነበር ። አቅም የሚጠይቁ ሥራዎች ያለጊዜው አይሆኑም። በቆሎ ትምህርት ቤት ደሳሳ ጎጄ ለመሥራት እቸገር ነበር። ዛሬ ፎቆ ቤት ሰጥቶኛል።

እርግጥ ነው ምድራዊ ቁስ ብዙ አያስደስትም። ይህ ደግሞ የሚታወቀው ሲደረስበት ነው ። ቁስ ደስታን አያመነጭም እንጅ ለሰው የሚያስፈልገው ሁሉ አለኝ። ምንም ሳይኖረኝ። በቆሎ ትምህርት ቤት የነበረችን ደስታ ግን አሁን የለችም። ያች ለተማሪ ምንም ለሌው የምትሰጥ ደገኛ ሀብት ናት። እሷን ሳስብ ቁስን እጸየፋለሁ።

ነገን ሳያስቡ ለመኖር ልጅነት ደጉ የቆሎ ትምህርት ቤት ወጉ ባህሉ ደስ ይላል።

እግዚአብሔር ለእኔ ብዙ አድርጎልኛል። በአንድ ወቅት የህክምና ጠበብቶች የዛሬን ቀን እንደማልደርስበት ሩቅ እንደሆነ ነግረውኝ ነበር። እኔ የሰማሁት ወዳጆቼ አይስሙት አልኩ። እንዳልኩት ሆነ። አስፈሪ ነገር መንገር ጥሩ አይደለም።

ዛሬ ያ ተለውጧል፣ የህክምና ጠበብቶቹን አስገርሟል። ሞያቸው ተጠራጠሩት። እውነቱ ግን የመድኃኔዓለም ቸርነት ነበር። ዋሽን እንዲ እንዲሉ አደረጋቸው። የእኛ ጌታ፣እሳቱን ውሃ፣ውሃን መርከብ ማድረግ ያውቅበታል። እነሱ እራሳቸው ሲጠራጠሩ እኔ እግዚአብሔር አመሰገንኩ። የቀደመልኝ እሱ ነዋ። መርማሪው እሱ ነበር።

ሃሳባቸው ላለመቀየር ደጋግመው ቢመራመሩ እኔ ግን የእግዚአብሔር ነበርኩ የሚሳነው የለም ብዬ የማምን የቀድሞውን ውጤት ሲነግሩ ብዙ እንደደከሙት ሳይሆን ሁለተኛውን ሲናገሩ እንደባህላቸው በአያቴ ስም ጠርተው አንተ እድለኛ ነህ ያሉኝ። ዛሬን እዳከብር ።ሌላ እድሜ ተጨምሮልኝ ስለነበር ነው።

#በእውነቱ የእግዚአብሔር ቸርነት እንጅ እኔ የተለየ ጭማሬ የሚደረግልኝ ሁኖ አይመስለኝም። በጨመረልኝ ቁጥር የሚጠብቅብኝ ሥራ አለብኝ ማለት ነው።

መልካም መሥራትን የመሰለ የለም። ከባዱ ፈተና እንደዮናስ ፈሪ የሚያደርገው ፣ መልካም ሥራ በህዝቦች መካከል የሚገለጥ ነው። ህዝባችን መልካም ሥራ በእራሱ አስተሳሰብ ልክ ወስኖታል። ለአንዱ መልካም የሆነው ሌላው ክፉ የሆናል። ለአንዱ ብትሰጥ ለምን ሰጠኽው ብሎ የሚከፋ፣አንዱን ብታመሰግን ለምን ታመሰግናለህ የሚል የአንተ ነጻነት የሚጋፋ አስተሳሰብ ስር እየሰደደ ነው። መልካም መሥራቱ ሳይከብድ እከሌን ይከፋው ይሆን ብሎ በተቃራኒው ጎራ ሆኖ ማስብ ከባድ ነው። እንደምታስቡት ቀላል አይደለም። ሞክሬው መክበዱን አይቻለሁ።

ጌታ ሆይ በጨምርክልኝ ዘመን። ማንንም ሳላስከፋ ምን ላድርግ?። በእውነት አንተ ግልጽልኝ እንጅ በእኔ መረዳት ዓለም በብዙ መልኩ አስቸጋሪ ሁናለች።

#ጌታ ሆይ የጨመርክልኝ ዕድሜና ዘመን ፣የደስታ ፣የንስሓ አድርግልኝ። ለአንተ ሁሉ ይቻላልና፣ እኔም ሁሉንም ማድረግ እንደምትችል ምስክር ነኝና የወደድከውን አድርግልኝ።
#እኔ የምወደውንና የምፈልገውን የዛሬውን ብቻ ሳይሆን የነገውንም አንተ ታውቃለህና የወደድከው ይሁን።

01/21/2026
"የመቀዳደም ጉዳይ ነው እንጂ ሞት ደጃችን ነው። ልባችን ገራገር ይሁን። ከክፋት እንራቅ። በጎ እናስብ"::
01/21/2026

"የመቀዳደም ጉዳይ ነው እንጂ ሞት ደጃችን ነው። ልባችን ገራገር ይሁን። ከክፋት እንራቅ። በጎ እናስብ"::

12/28/2025

እንኳን ለመላዕኩ ቅዱስ ገብረኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን ::
ታኅሣሥ 19 ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን በባቢሎን አገር ከነደደ እሳት ውስጥ በጨመሩአቸው ጊዜ ያዳናቸው ቀን ነው፡፡

እኛንም እንደ እሳት ከሚያቃጥል ኃጢአት ይጠብቀን፡፡🙏

«እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብረኤል ነኝ » እንዳለው በቃሉ ለካህኑ ዘካርያስ፡፡ እኛም በዝማሬ ፡፡
ገብረኤል ሀያል መላከ ሰላም
መላከ ብስራት የምታወታ
የ እግዚአብሔርን ህዝብ ከሚነድ
እሳት ፍቅርህ ተስሏል በልባችን
ፊትህ ቆመናል ባርከበ ብለን
አሜን፡፡

12/26/2025

በአማራ ክልል በሚደረጉ ስብሰባዎች አንዳንድ ተጎጆች የደረሰባቸውን ሰቆቃው ስሰማ ፣ለእራሴ ክብር ሰጥታቸለሁ።

ጦርነት አውዳሚ ፣ነጻነት ሳይሆን ሌላ ባርነት ነው በሚል አጥብቄ ከመጀመሪያው ጀምሮ ተቃውሞ አስምቻለሁ።

ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት በክልሉ በሄድኩበት ጊዜ አንዳንድ የታጣቂ ሃላፊዎችን አግኝቼ ሳነጋግር የነገርኳቸው እውነት ይህን ነበር።

የመንግሥት ተወካዮቹ በእየቦታው ብሶት ሲያሰሙ፣ ተው ይህን ሕዝብ የባሰ ጣጣ እንዳታስገቡት የሚል ጽኑ ምክር መስጠቴን አስታውሳለሁ።

ሁሉም አልተደሰቱብኝም ነበር። በውጭ ሀገርማ ብዞቹ የመንግሥት ደጋፊ አድርገው ወቅሰውኛል።

በዘመነ ወያኔም እንደአሁኑ ሶሻል ሚዲያ ባይኖርም፣በነበሩ ወብሳይቶች ደጋፊ ተብየ መወቀሴን አረሳውም።

ወያኔ ወደ ጦርነት ሲገባም፣ እርግማን መሰል የብስጭት ጽሑፍ መጻፌን አረሳውም። ለትግራይ ገበሬ ጦርነት አይገባውም ። ይበቃዋል ከተማ ተመችቷችሁ ፣ልጆቻችሁን ውጭ አስቀምጣችሁ ለጦርነት አትጋብዙ ብዬ ስጽፍ ብዙ ትግረኛ ተናጋሪዎች ተራ ስድብ ሳይቀር ሰደቡኝ።

ዛሬ ብዙ ወጣቶች ትላንት እኔ እንደምቃወመው መቃወም ጀምረዋል። ብዙ ትግረኛ ተናጋሪዎች ከሠራ ሲፈናቀሉም ጽፌአለሁ። ምን አገባህ የመከላከያ ደጋፊ ብለው ወቀሱኝ። የሀገር መከላከያ ተቋም ነው። ግለሰብ አይደለም። ጠንካራ ተቋም ቢኖር አሁን ያለው ሥራዓተ አልበኝነት አይኖርም ነበር።

መደገፍ ብቻ ሳይሆን በጸሎቴም ጠንካራ ተቋም እንዲሆን አስበዋለሁ። ቢሆንም ደስ ይለኛል። ይህ በመጽሐፍም ያለ አባቶቻችን ያቆዩን ሥርዓተ እምነት ነው።

በጊዜያዊ ችግር ተቋምን ለውጬ አላውቅም ። አማራ ያልበላውን እዳ እየከፈለ ነው።

የአለፈ የአገደመው እንጅራውን ይጋግርበታል። ሲሞላለት ጠላት ይሆነዋል።
አሁን በአማራ ስም ሶሻልሚዲያው ላይ ያሉትን ብዞቹ፣ስንት ጊዜ አቋማቸው ቀያየሩ ለምን? ብሎ የጠየቀ እውነቱን ለማወቅ ጉዞ ይጀምሯል።

ወዳጄ አማራ ክልል ፣አሁን እየተነገረ ያለው ትንሹ ነው። ሁሉንም ብትሱሙ ፣ እውነት ሰው ነን?፣ ምን ነክቶነው? ትላላችሁ።?

መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት በዚያ ክልል ያሉ ሃላፊዎች እስር ቤት የሚያስገባ፣ እኛንም ወጥተን ኡኡኡ ያላልነውን ምን ነክቶን ነው? የሚያሰኝ የህሊና ክስ ያቀርባል።

በእራሱና በሚመራው ሕዝብ የሚቆምር አስተዳደር ፣ ፍርዱ ከሰማይ ቢሆንም አንድ ቀን ህዝብን አነሳስቶ የነበረውን እንዳልነበር ያደርገዋል።

እኔ ግን በማየውና በምሰማው ባዝንም፣ ህሊናዬ ከእውነት ጋር ስለዋለ ከወቀሳ ነጻ ነኝ።

አንተ ሕዝብ ቀለብ ሰፍረህ እንደ ልጅ የአስተማርከኝ። እንደ ልጅህ እንጀራ ቁርሰህ የመገብከኝ። መከራህ ብዝቶ ምንም ሳላግዝህ በመቅረቴ ጸጸቴን እየገጥኩ። እግዚአብሔር ሠላሙን ያጣልህ።
ለአንተ ይህ አይገባም ነበር በማለት ቁጭቴን ለታሪክ አኖርኩ።

🙏🙏🙏❤️❤️❤️እንኳን ለኅዳር ጽዮን አመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤አደረሰንእግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታል !“ጽዮን” የሚለው ቃል ትርጓሜው “ጸወን አምባ መጠጊያ” ማለት ነው፡፡ አንድም በምሥጢሩ ሲ...
11/30/2025

🙏🙏🙏❤️❤️❤️

እንኳን ለኅዳር ጽዮን አመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤አደረሰን

እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታል !

“ጽዮን” የሚለው ቃል ትርጓሜው “ጸወን አምባ መጠጊያ” ማለት ነው፡፡ አንድም በምሥጢሩ ሲፈታ “ማሕደረ አምላክ” ማለት ነው፡፡ ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል፡፡

“እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ። ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ። አሮጊቶችዋን እጅግ እባርካለሁ፥ ድሆችዋንም እንጀራ አጠግባለሁ። ካህናቶችዋንም ደኅንነትን አለብሳቸዋለሁ፥ ቅዱሳኖችዋም እጅግ ደስ ይላቸዋል።” የሚል ኃይለ ቃል በመዝ 131÷13 ተጽፎ እናገኛለን፡፡ ኅዳር 21 ቀን ጽዮን ማርያም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል ነው፡፡ በዚህ ቀን ታቦተ ጽዮን፣ ጽላተ ኪዳን ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን።

በሊቀ ካህኑ ኤሊ ዘመን ታቦተ ጽዮን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ ኢሎፍላውያን እጅ ተማረከች፡፡ እነርሱም ታቦተ ጽዮንን ዳጐን በተባለው ጣኦታቸው ቤት ውስጥ አመሻሽ ላይ ታቦቷን ከስር ጣኦቱን ከላይ አድርገውት ቢሔዱም ማለዳ ሲመጡ ዳጎንን ጥላው በላዩ ላይ ተቀምጣበት አገኙ፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ እንደቀድሞው ቢያስተካክሉም በሦስተኛው ቀን ግን መሬት ላይ ጥላው በግንባሩ ተደፍቶ ሲሰግድላት አጊኝተውታል፡፡

ሀገራቸው በእባጭ በሽታ በመመታቱም ታቦተ ጽዮንን ከእጅ መንሻ ጋር ወደ ሀገሯ ሸኝተዋታል፡፡ 1ኛ ሳሙ. 5÷1 ተጽፎ የምናገኘው ይሕ ታሪክ በየዓመቱ ኅዳር 21 በደማቅ ሥነ ስርዓት በአክሱም ጽዮን ይከበራል፡፡ በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ፤ አገለገለ።

ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት። በዚህም ምክንያት ሚስቱ ሜልኮል ንቃው ማኅጸኗ ተዘግቷል እስክትሞትም ደረስ አልወለደችም ነበር እንዲል። ይህንም በ1ኛ ዜና መዋዕል 15÷23 ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡ በቅዱስ ሰሎሞን፣ መፍቀሬ ጥበብ ዘመንም ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ሆኖ ነበር። እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሱን አነጋግሮ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ንጉስ ሚኒሊክ ዕብነ ሐኪም ታቦተ ፅዮንን ይዞ ገብቷል።

በዘመነ አፄ ባዜን በ4ኛው መ.ክ.ዘ አማናዊት ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ፅዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህም ጊዜ ሁለቱ ጽዮኖች ታቦተ ጽዮንና ጽዮን የምትባል ቅድስት ድንል ማርያም ሲገናኙ አክሱም ከክብራቸው የተነሳ በብርሃን አሸብርቃለች። በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአፅብሓ ዘመን አስራ ሁለት መቅደስ ያሏትን ቤተ መቅደስ ለእመብርሃን ሰርተዋል በጌታችንም ተቀድሷል።

በአረመኔዋና የቤተ ክርስቲያን ቀንደኛ አውዳሚ በሆመችው በዮዲት ጉዲት ቤተ መቅደሷ ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር በኋላም ቤተ መቅደሷ ሲሰራ ተመልሳ እንደመጠችም በኅዳር 21 ቀን ትከበር ነበር። ኅዳር 21 ቀን በደማቅ ስነስርዓት ስናከብር እነዚህን ድንቅ ተአምራትና ታሪኮች እናስባለን። እንግዲህ ከፍጡራን ሁሉ በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነች እናታችንን ስናስብ "ቅድስት" ማለታችን እንደሌሎች ቅዱሳን በእኩል ደረጃ እያሰብን ሳይሆን ትርጉሙ ይለያል፣

የእርሷም ቅድስና ልዩ ነውና ቅድስተ ቅዱሳን ንፅሕተ ንፁሓን ብርክት እምብሩካን ኅሪት እምኅሩያን እያልን እንጠራታለን።

ገዳማውያኑም ዘወትር ጽዮን እናታችን ሆይ ምልጃሽ አይለየን፣ ጥበቃሽ አይራቀን እያሉ ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጸና ከበረከታቸው እንሳተፍ፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:-
ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:-
09 38 64 44 44
0918077957

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

Address

Washington D.C., DC

Opening Hours

Monday 9am - 5pm
Tuesday 9am - 5pm
Wednesday 9am - 5pm
Thursday 9am - 5pm
Friday 9am - 5pm
Saturday 9am - 5pm

Telephone

+251913023588

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia African posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share