Addis Monitor

Addis Monitor Addis Monitor helps you cut through the noise !

Addis Monitor is USA based News Network that provides videos of news everyday on politics, entertainment and showbiz in fun and simple manner for the Ethiopian community all around the world.

ሮይተር ያሰራጨው ዘገባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረታዊ መመሪያን ያላገናዘበ መሆኑም የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሰረት ዜጎች ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱ የቀበሌ...
11/12/2021

ሮይተር ያሰራጨው ዘገባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረታዊ መመሪያን ያላገናዘበ መሆኑም የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ


በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሰረት ዜጎች ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱ የቀበሌ መታውቂያ መያዝ አለባችው ቢልም ሮይተር ያወጣው ዘገባ ሰዎች በማንነታቸው ለመለየት
እንደሆነ አድርጎ የሰራው ዘገባ ከእውነታ ያራቀና አግባቡነት የሌለው መሆኑን የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል
ሮይተር በሰራው ዘገባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረታዊ መመሪያን ያላገናዘበና ከአዋጁ አተገባባር ጋር የሚጻረርና አግባብነት የሌለው ነው ብሏል፡፡
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዜጎች ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱ የነዋሪነት መታወቂ፣ መንጃ ፍቃድና የሠራተኛ መታወቂ ሳይዙ መንከሳቀስ የተከለከለ መሆኑን መደንገጉ ይታወሳል፡፡

ለ21 ቀናት በእስር የቆየችው የአሃዱ ሬድዮ ጋዜጠኛ፤ በዋስትና ተፈታች21 ቀናት በእስር ላይ የቆየችው የአሃዱ ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ ሉዋም አታክልቲ፤ በአስር ሺህ ብር ዋስትና ዛሬ አርብ ከእስር ...
11/12/2021

ለ21 ቀናት በእስር የቆየችው የአሃዱ ሬድዮ ጋዜጠኛ፤ በዋስትና ተፈታች
21 ቀናት በእስር ላይ የቆየችው የአሃዱ ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ ሉዋም አታክልቲ፤ በአስር ሺህ ብር ዋስትና ዛሬ አርብ ከእስር ተፈታች። የጣቢያው ዜና አርታኢ የሆነው ጋዜጠኛ ክብሮም ወርቁም፤ በ15 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈታ በፍርድ ቤት መወሰኑን የጋዜጠኞቹ ጠበቃ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ይግባኝ ሰሚ ችሎት፤ ጋዜጠኛ ሉዋም በዋስትና እንድትፈታ የወሰነው ከሶስት ቀን በፊት ማክሰኞ ጥቅምት 30፤ 2014 ነበር። ሆኖም “በአሰራር አለመናበብ ችግር ምክንያት” እስከ ዛሬ ስድስት ሰዓት ድረስ ሳትፈታ በእስር መቆየቷን ጠበቃዋ አቶ ጥጋቡ ገልጸዋል።
ጋዜጠኛዋ በእስር ወደ ቆየችበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ጠዋት የሄዱት ጠበቃዋ፤ “የፌደራል ፖሊስ በሌላ ጉዳይ ይፈልጋት እንደሆነ ማጣራት እንዲደረግ” በሚል ወደዚያው መላኳ እንደተነገራቸው ጠቅሰዋል። የፌደራል ፖሊስ ጋዜጠኛዋን በሌላ ጉዳይ እንደማይፈልጋት ካሳወቀ በኋላ፤ ሉዋም ዛሬ ምሳ ሰዓት ገደማ ከእስር ተፈትታ ከቤተሰቦቿ ጋር መቀላቀሏን አቶ ጥጋቡ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦

– የጣቢያው ዜና አርታኢም በዋስትና እንዲፈታ በፍርድ ቤት ተወስኖለታል በሃሚድ አወል ለ21 ቀናት በእስር ላይ የቆየችው የአሃዱ ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ ሉዋም አታክልቲ፤ በአስር ሺህ ብር ዋስትና...

ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት  ጥሪ ቀረበጥቅምት 26/2014 (ዋልታ) የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት ጥሪ አቀረበ፡፡የጥሪ ማስታወቂያው ሙሉ ዝርዝርቀጥሎ ቀ...
11/05/2021

ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት ጥሪ ቀረበ
ጥቅምት 26/2014 (ዋልታ) የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት ጥሪ አቀረበ፡፡
የጥሪ ማስታወቂያው ሙሉ ዝርዝርቀጥሎ ቀርቧል፡-
በሃገራችን እየተደረገ ያለውን ሃገርን የማፍረስ ሴራን በማክሸፍ አገርን የማዳን ዘመቻ ላይ ባላቸው እውቀት ልምድ እና አቅም ከአገር መከላከያ ሠራዊት ጎን በመሰለፍ ይህ አፍራሽ ሃይል እስኪደመሰስ ድረስ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ባላቸው ተነሳሽነት ከሀገር መከላከያ ጎን በመቆም አቅማቸውና እውቀታቸው የፈቀደውን አስዋፅኦ ለማበርከት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
በዚሁ መሠረት ይህንን ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል አካላዊ ሁኔታ ፣ የጤና ፣ የስነ - አእምሮ ዝግጁነት ፣ እውቀት እና ልምድ ያላቸውን አባላት ከዚህ በታች የተቀመጠውን መስፈርት ለሚያሟሉ የቀድሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የወጣ መስፈርት፡፡
1. አጠቃላይ መስፈርቶች
1.1. የኢፊዴሪ ሀገ - መንግስትን የተቀበሉ ፣
1.2. በህዝቦች ሉአላዊነትና አንድነት የሚያምኑ እና በፅናት ለማገልገል
ሙሉ ፍቃደኝነት ያላቸው ፣
1.3. ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ የሆኑ ፣
1.4. በወንጀል ይሁን በፍታብሄር ተከሶ የፍርድ ቤት ክርክር የሌለባቸው፣
1.5. መከላከያ የሚያሰማራቸው የጦር ክፍሎች ሁሉ ተዘዋውረው
ለመስራት ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑና የአካል ብቃት ያላቸው ፣
1.6. ለእግረኛ አዋጊ መኮንኖች ፣ ሻለቃ አመራርና ከዚያ በላይ ሃላፊነት
የነበራቸው፣
1.7. በየትኛውም የማዕረግ ደረጃ ላይ በየማሰልጠኛ ማዕከላት አሰልጣኝ
የነበሩ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፣
1.8. የሜካናይዝድ እና የቡድን መሳሪያ አመራርና ምድብተኛ የነበሩ ፣
1.9. የጤንነት ሁኔታን በተመለከተ
 የአይን ፣ የአፍንጫ ፣ የጆሮ ፣ የጥርስ ፣ የከንፈር ፣ ችግር የሌለባቸው ፣
 ከቲቢ ፣ ከሚጥል በሽታ ፣ ከስኳር ፣ ከደም ግፊት ፣ ከኪንታሮት ፣
ከእንቅርት በሽታዎች ነፃ የሆኑ እና ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የሆነ
አካላዊ ችግር የሌለባቸው ( የማያነክስ ) ፣
1.10. የትምህርት ሁኔታ ማቀድ ፣ ማሠልጠን ፣ የስልጠና ዶክሜንት
ማዘጋጀት የሚያስችል የትምህርት ዝግጅት ያለው ፣
1.11. በሚመለመልበት አካባቢ ከቀበሌ ፣ ከመስተዳድር እና ከፖሊስ
ከወንጀል ነፃ ስለመሆናቸው የፅሁፍ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፣
1.12. የቀድሞ ጦር ሠራዊት አባል ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ
የሚችሉ ፡፡
2. ዕድሜን በተመለከተ፡-
2.1. ከወታደር እስከ ከፍተኛ የበታች ሹም ያሉ ከ55 ዓመት
ያልበለጡ ፣
2.2. መስመራዊ መኮንኖች ከ60 አመት ያልበለጡ ፣
2.3. ከሻለቃ በላይ ያሉ ከፍተኛ መኮንኖች ከ64 ዓመት ያልበለጡ
መሆን አለባቸው፡፡
3. የምልመላ ቦታና ጊዜ ፡-
 ለአዲስ አበባ ተመዝጋቢዎች በየክፍለ ከተማቸው ሲሆን
 ለክልል ተመዝጋቢዎች በየአካባቢያችሁ ባሉ የቀበሌ ፣ የወረዳ
አስተዳደርና የፀጥታ ወይም ሚሊሻ ፅ/ቤት በአካል በመቅረብ
መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ፣
 የምዝገባ ጊዜው ከህዳር 01 ቀን 2014 ዓ/ም እስከ ህዳር 15 ቀን 2014 ዓ/
ም ድረስ ይሆናል፡፡
 በሁሉም የምዝገባ ጣቢያዎች ዝርዝር መስፈርቶች ተለጥፎ የሚገኙ
መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የአገር መከላከያ ሚኒስቴር
ጥቅምት 2014 ዓ/ም
አዲስ አበባ

አሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔን የሚያወግዝ ሰልፍ በተለያዪ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች እየተካሄደ ነው! አሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔን የሚያወግዝ ሰልፍ አዳማን ጨምሮ በተለያዪ የኦሮሚያ ክልል ከተሞ...
11/05/2021

አሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔን የሚያወግዝ ሰልፍ በተለያዪ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች እየተካሄደ ነው!
አሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔን የሚያወግዝ ሰልፍ አዳማን ጨምሮ በተለያዪ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች እየተካሄደ ነው::
የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ድጋፍም በሰላማዊ ሰልፉ ገልፀዋል::
የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. የተሰውትን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጀግኖችን ለመዘከር ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ገልፀዋል፡፡
እየተካሄደ ባለው ሰላማዊ ሰልፍ የሸብር ቡድኖቹን ድርጊት የሚያወግዙ እና የህልውና ዘመቻውን የሚደግፉ መልዕክቶች እየተላለፉ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
አካባቢህን ጠብቅ‼
ወደ ግንባር ዝመት‼
ሠራዊቱን ደግፍ‼

ደቡብ ጎንደር ወደ ግንባር ከተተአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ጎንደር ሕዝባዊ ሠራዊት የቀረበለትን የክተት ጥሪ ተቀብሎ ወደ ግንባር ከቷል። የአማራ ሕዝብ የመኖር...
11/05/2021

ደቡብ ጎንደር ወደ ግንባር ከተተ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ጎንደር ሕዝባዊ ሠራዊት የቀረበለትን የክተት ጥሪ ተቀብሎ ወደ ግንባር ከቷል።
የአማራ ሕዝብ የመኖር ሕልውና አደጋ ላይ ወድቋልና ለቀረበለት የክተት ጥሪ ፈጣን ምላሽ ሰጥቷል። ሕዝባዊ ሠራዊቱ የአማራ ሕዝብን አዋርዶ፣ ዘርፎና ገድሎ ኢትዮጵያን ለመበታተን የተነሳውን አሸባሪ ህወሓት ሳያጠፋ ወደ ቤቱ ላይመለስም ተማምሏል።
በመርኃ ግብሩ የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ሲሳይ ዳምጤ፥ የሕልውና ዘመቻው የአማራ ክልልን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን እስከመጨረሻ ነጻ ለማውጣት እንደሆነ አብራርተዋል።
አቶ ሲሳይ እንዳሉት ጠላትን ማጥፋት የዘመቻው መዳረሻ ነው።
በሁሉም ግንባሮች ጠላት ዳግም በማያንሰራራበት ደረጃ ለመምታት ዝግጅት መደረጉን በመግለጽም መንግሥት ለዘማቾች አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኀላፊ ቀለመወርቅ ምህረቴ በበኩላቸው ዘማቾች ታሪክ እየሠሩ ካሉት የመከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይል፣ የፋኖ፣ የሚሊሻ አባላት እና የአማራ ሕዝብ ጋር ተሰልፈው ተልዕኳቸውን በጀግንነት እንዲወጡም አስገንዝበዋል።
ሀገርን እና የአማራን ሕዝብ ነጻ ለማውጣት የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ተቋቁሞ በጽናት መዋጋትና ማሸነፍ ብቸኛው አማራጭ ነው ያሉት ደግሞ የዞኑ ዋና አሥተዳዳሪ ይርጋ ሲሳይ ናቸው።
የሁሉም ወረዳ የፖለቲካ መሪዎች፣ ሚሊሻዎች፣ የፖሊስ አባላት እና ልምድ ያላቸው ምልስ የሠራዊት አባላት የመሪነት ሚናውን በአግባቡ እንደሚወጡ ተናግረዋል።
የሚሰጡ መመሪያዎችን አክብረው እንዲንቀሳቀሱ መልዕክት ማስተላለፋቸውን አሚኮ ዘግቧል።

የፌዴራል ፖሊስ  ጥቆማ መስጫ የስልክ  መስመሮች ማንኛውም  የፀጥታ  ችግር  እንቅስቃሴ  ሲመለከቱ  በነዚህ  የስልክ መስመሮች ፈጥነው ይደውሉ። ጥቆማ በመስጠት ይተባበሩን ሲል ፖሊስ  ጥሪ ...
11/04/2021

የፌዴራል ፖሊስ ጥቆማ መስጫ የስልክ መስመሮች

ማንኛውም የፀጥታ ችግር እንቅስቃሴ ሲመለከቱ በነዚህ የስልክ መስመሮች ፈጥነው ይደውሉ።

ጥቆማ በመስጠት ይተባበሩን ሲል ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

 ሱዳን በየአቅጣጫው መንደድ ጀምራለች።መፈንቅለ መንግስቱን የመራው የሱዳን ወታደራዊ መሪየግብፅ ተላላኪውና በኢትዮጵያ ተደጋጋሚ ወረራየፈፀመው አብዱልፈታህ አልቡርሃን በሱዳን ብሔራዊቴሌቭዥን ቀ...
10/25/2021


ሱዳን በየአቅጣጫው መንደድ ጀምራለች።
መፈንቅለ መንግስቱን የመራው የሱዳን ወታደራዊ መሪ
የግብፅ ተላላኪውና በኢትዮጵያ ተደጋጋሚ ወረራ
የፈፀመው አብዱልፈታህ አልቡርሃን በሱዳን ብሔራዊ
ቴሌቭዥን ቀርቦ ንግግር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የሱዳን ህዝብ በተቃራዊ አመፅ አስነስቷል ፣ መንገዶችን
ዘግቷል ፣ ቡርሃን አይመራንም እያለ ነው።

ሻንጋይ ፋርማ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሊያደርግ ነው።በቻይና ሀገር 2ኛው ግዙፍ የመድሃኒት አምራች እና አካፋፋይ "ሻንጋይ ፋርማ /Shanghai Pharma/ ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ ወ...
10/23/2021

ሻንጋይ ፋርማ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሊያደርግ ነው።

በቻይና ሀገር 2ኛው ግዙፍ የመድሃኒት አምራች እና አካፋፋይ "ሻንጋይ ፋርማ /Shanghai Pharma/ ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ ወስኗል።

ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የአዋጭነት ጥናት ካጠናቀቀ በኋላ ነው ኢንቨስት ለማድረግ ውሳኔ ላይ የደረሰው።

የሻንጋይ ፋርማ ኩባንያ ተወካዮች ከአንድ ሳምንት በፊት በቻይና ከኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

የሻንጋይ ፋርማ ኢትዮጵያ ሥራ አስኪያጆች በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዝነኛው አሜሪካዊ ተዋናይ አሌክ ባልድዊን በፊልም ቀረጻ ወቅት ለቀረጻ ተብሎ የተዘጋጀ መሳሪያ ተኩሶ አንዲት ሴትን ገደለ።ተዋናይ አሌክ ባልድዊን በፊልም ቀረጻ ወቅት መደበኛ የጦር መሣሪያ ያል...
10/22/2021

ዝነኛው አሜሪካዊ ተዋናይ አሌክ ባልድዊን በፊልም ቀረጻ ወቅት ለቀረጻ ተብሎ የተዘጋጀ መሳሪያ ተኩሶ አንዲት ሴትን ገደለ።

ተዋናይ አሌክ ባልድዊን በፊልም ቀረጻ ወቅት መደበኛ የጦር መሣሪያ ያልሆነ፣ ለፊልም ቀረጻ የሚያገለግል መሳሪያ ከተኮሰ በኋላ አንዲት ሴትን ገድሎ ሌላ አንድ ተጨማሪ ሰው አቁስሏል።

ፖሊስ እንዳለው ባልድዊን መሣሪያውን የተጠቀመው ለሴንቸሪ ዌስተርን ረስት ፊልም በሚቀረጽበት ወቅት ነው።

ጉዳት የደረሰባት ሴት ሆስፒታል ብትወሰድም በደረሰባት ጉዳት ህይወቷ አልፏል። ጉዳት ያጋጠመው የፊልሙ ዳይሬክተር ሕክምና እየተደረገለት ይገኛል።

የተዋናይ ባልድዊን ቃል አቀባይ ለኤፒ የዜና ወኪል እንደተናገረው ክስተቱ የተፈጠው ባዶ መሆን የነበረበት መደበኛ ያልሆነው መሳሪያ በስህተት ከተተኮሰ በኋላ ነው።

ህይወቷ ያለፈው የ42 ዓመቷ ሃልይና ሁትቺንስ የምትባል ሲሆን የፎቶግራፍ ዳይሬክተር ሆና ታገለግል ነበር ተብሏል። ህክምና እየተደረገለት ያለው የፊልሙ ዳይሬክተር የ48 ዓመቱ ዮኤል ሱዛ ነው።

ዝነኛ በሆነው የፊልም ቀረጻ ሥፍራ ቦናንዛ ክሪክ ራንች ስለተፈጠረው ክስተት ፖሊስ ምርመራውን እያካሄደ ሲሆን እስካሁን ምንም ክስ አልተመሰረተም።

የአካባቢው ጋዜጣ ሳንታ ፌ ኒው ሜክሲካን እንደዘገበው የ68 ዓመቱ ባልድዊን ሐሙስ ዕለት እያለቀሰ በአካባቢው የፖሊስ ቢሮ መታየቱን ዘግቧል።

የግል ድረ-ገጿ እንደሚኣሳየው፣ ሟች ሁትቺንስ ከዩክሬን የመጣች ሲሆን ያደገችው በሶቪዬት ወታደራዊ ካምፕ ነው። በኪዬቭ ጋዜጠኝነትን በሎስ አንጀለስ ደግሞ ፊልም ተምራለች። እአአ በ2019 ላይ በአሜሪካ ሲኒማቶግራፈር መጽሔት ተስፋ ያላት ባለሙያ ተብላ ተሸልማ ነበር።

በአዳም ኢጂፕት ሞርቲመር ለሚመራው እና በድርጊት የተሞላ ፊልም ሁትቺንስ ሃልይናን ፊልም፣ የፎቶግራፍ ዳይሬክተር ነበረች።

የዓለም አቀፉ ሲኒማቶግራፈር ጊልድ ለቫሪቲ መጽሔት በሰጠው መግለጫ የሁትቺንስን ሞት "አሳዛኝ ዜና እና አስከፊ ኪሳራ" ብሎታል።

ባልድዊን የፊልሙ ተባባሪ ፐሮዲዩሰር ሲሆን የ13 ዓመት የልጅ ልጁ በድንገተኛ ግድያ የተፈረደበት ግለሰብ ገጸ ባህሪን ይዞ ይተውናል።

በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በሙት ባሕር አካባቢ የአየር ንብረት ለውጥን ተጽዕኖ ለማጉላት በማሰብ ርቃናቸውን በመሆን ፎቶ ተነስተዋል።
10/21/2021

በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በሙት ባሕር አካባቢ የአየር ንብረት ለውጥን ተጽዕኖ ለማጉላት በማሰብ ርቃናቸውን በመሆን ፎቶ ተነስተዋል።

ስለ ሐይቅ ከተማ መረጃ! ትናንት ማምሻውን ሐይቅ ከተማ በጠላት እጅ እንደወደቀች ተደርጎ በአንዳንድ የጠላትን አጀንዳ በሚያራግቡ ቅጥረኛ ኃይሎች ሲቀርብ የነበረው የበሬ ወለደ አሉባልታ ሀሰት ...
10/21/2021

ስለ ሐይቅ ከተማ መረጃ!
ትናንት ማምሻውን ሐይቅ ከተማ በጠላት እጅ እንደወደቀች ተደርጎ በአንዳንድ የጠላትን አጀንዳ በሚያራግቡ ቅጥረኛ ኃይሎች ሲቀርብ የነበረው የበሬ ወለደ አሉባልታ ሀሰት ነው።
ሐይቅ ከተማ አሁንም በሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በአማራ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ቁጥጥር ሥር ስትሆን የደቡብ ወሎ ዞን፣ የተሁለደሬ ወረዳና የሐይቅ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ከጸጥታ ኃይሉ ጋር ተቀናጅተው አመራር በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
አሸባሪው፣ ጨፍጫፊው፣ ዘራፊውና ወራሪው የትግራይ ኃይል በውጫሌ፣ ተሁለደሬ፣ ወረባቦና ደላንታ ግንባሮች ጦርነት የከፈተብን ቢሆንም ህዝባችን ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመቀናጀት ሰርጎ ለመግባት እየሞከረ ያለውን ወራሪ ኃይል ወደ ቀሪ አካባቢዎች እንዳይገባ በአንድነት በመዝመት መመከት እንዲሁም አካባቢውን ከጸጉረ ልውጥ በመጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን።

የኢትዮጵያ አየር ሀይል በመቀሌ ከተማ የሚገኙ ወሳኝ የህወሓት ወያኔ የጦር ማከማቻውችን እና መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ አጠገብ ያለን ዴፓን ደብድቧል! በተጨማሪም እንደመረጃው ከሆነ የኢትዮጵያ አየ...
10/20/2021

የኢትዮጵያ አየር ሀይል በመቀሌ ከተማ የሚገኙ ወሳኝ የህወሓት ወያኔ የጦር ማከማቻውችን እና መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ አጠገብ ያለን ዴፓን ደብድቧል! በተጨማሪም እንደመረጃው ከሆነ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢላማውን መቶ በመቶ ባሳካ መልኩ ከባድ ጥቃት በማድረስ ጁንታው ላይ ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል የኢትዮጵያ አየር ሃይል ዛሬ ጥቅምት 10 ረፋድ ላይ በመቐለ ከተማ በተመረጡ ኢላማዎች በተሳካ መልኩ መቷል።
የኢትዮጵያ አየር ሃይል ዛሬ ኢላማ አድርጎ የመታው የአሸባሪው ህወሓት የጦር መሳርያ መጋዝኖች ናቸው።
በመቐለ ከተማ ውስጥ በርከት ያሉ ጦር ማከማቻዎች እና የወታደራዊ ማሰልጠኛዎች እንዳሉ ይታወቃል።
ጀግና የኢትዮጵያ አየር ሃይል ከሁለት ቀን በፊትም በመቐለ የነበረ የአሸባሪው ህወሓት መገናኛ ዘዴዎች በተሳካ መንገድ መምታቱ ይታወቃል። ጀግናው የኢትዮጵያ አየር ሃይል ታርጌት የተደረጉ ቦታዎች ሲመታ ጥንቃቄ በተሞላው ነው።
አየር ኃይላችን እየወሰደ ባለው አስደናቂ የአየር ጥቃት ሰላማዊ ሰዎችን በማይጎዳ መልኩ ለሶስተኛ ግዜ በከፍተኛ ጥንቃቄ ስኬታማ ኦፕሬሽን እያካሄደ ነው…

Address

4853 7th Street NW
Washington D.C., DC

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Monitor posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Monitor:

Share

Addis Monitor helps you cut through the noise!

Addis Monitor is an Infotainment channel that provides videos of news everyday on politics,entertainment and showbiz in fun and simple manner for the ethiopian community all around the world. Addis Monitor helps you cut through the noise and understand what's driving events in the headlines and in our community.