01/21/2022
በቀለ ለገሰ ተከሰሰ
በአዲስ አበባ ከተማ የግለሰቦችን መሬት በጠራራ ጸሐይ ዶዘር አጥርና ቤታቸውን ያፈረሰውና በዚያው እለት የከተማ አስተዳደሩ በህገወጥ መንገድ ለዘረፈው መሬት ካርታ አውጥቶ የሰጠው በቀለ ለገሠ አረና ክስ ተመሰረተበት።
ባለንብረቶቹ ካሳም ሆነ ምትክ አልተሰጣቸው።
ግለሰቡ ባለፉት ሦስት ዓመታት ምንጩ ከየት እንደሆነ የማይታወቅ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚያንቀሳቅስና በቅጽል ስሙ ሌላኛው ድንቁ ደያስ በሚል የሚታወቀው በቀለ ለገሰ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ከነባር ባለይዞታዎችን ንብረት የሆነ መሬት በንጥቂያ በመውሰዱ ነው ክሱ የተመሰረተበት።
ይሄው ልቡ ያበጠውና በአፍቅሮተ ንዋይ ማጋበስ ሙስና የታወረው ግለሰቡ ባለንብረቶችንም በማሳሰር አሰቃይቷቸዋል።
በፌዴራል ፍርድ ቤት ክስ የተመሰረተው በዚሁ ግለሰብና በከተማ አስተዳደሩ ላይ ነው። የክሱን ይዘትና የተከሳሽን መልስ እንዲሁም በአስተዳደሩ ያሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች አስመልክቶ ማጠናቀር የጀመርነውን ሪፖርት እንዳጠናቀቅን በዚሁ ፔጅ በተከታታይ እናቀርብላችኋላን። like follow እንድታደርጉም እንጋብዛለን።