11/15/2025
#እሞትባችኋለሁ❗️ የወሰድኩትን 8.9 ቢሊየን ይቅር በሉኝ❗️
እኚህ ለህዝብ በቀጥታ እየተላላፈ ባለ የቴሌቭዥን ስርጭት ላይ በተቀመጡበት ወንበር ላይ ድፍት ያሉት ናይጄሪያዊው ፕሮፌሰር ዳንኤል ፖንዴይ ናቸው፡፡
#እሳቸው ደግሞ ማናቸው ካልክ…
ፕሮፌሰር ዳንኤል ማለት በናይጄሪያ በነዳጅ ሀብት የበለፀገው የኒጀር ዴልታ ክልል ልማትን ለማፋጠን የተቋቋመው የኒጀር ዴልታ ልማት ኮሚሽን (Niger Delta Development Commission - NDDC) ተጠባባቂ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ነበሩ፡፡
ይህ በእሳቸው የሚመራው ኮሚሽን በቢሊዮን የሚቆጠር የህዝብ ገንዘብ የሚያስተዳድር ሲሆን በሙስና ደግሞ በተደጋጋሚ ስሙ የሚነሳ ነበር፡፡
#ታዲያልህ…
ፕሮፌሰር ፖንዴይ ኮሚሽኑን ሲመሩ N81.5 ቢሊዮን የናይጄሪያ ናይራ ወይንም በእኛ አሁናዊ ምንዛሬ ስትመታው 8.9 ቢሊየን ብር ቆርጥመዋል በሚል ክስ ቀረበባቸው፡፡
የዚህን ሙስና ክስ ምርመራ ደግሞ የሀገሪቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኮሚቴ መያዙን ተከትሎ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት በማግኘቱ የፓርላማው ችሎት በቀጥታ በቴሌቪዥን እንዲተላለፍ ተወሰነ።
#ታዲያልህ…
ፕሮፌሰሩ በምክር ቤቱ ኮሚቴ ፊት ቀርበው ስለ ገንዘቡ እየተጠየቁ ባለበት ሰአት በድንገት ስልምልም… ዝልፍልፍ ብለው ራሳቸውን ስተው ወንበራቸው ላይ ወደቁ።
አንዳንዶች ፖንዴይ ጥያቄው ሲጠነክርባቸው የማንሾካሾክ በሚመስል ሁኔታ.. “እንዳልሞትባችሁ… እንዳትፀፀቱ.. እሞትባችኋለሁ!” ሲሉ ሰምተናል ሲሉ ተደመጡ፣ የፕሮፌሰሩን አሳዛኝ ሁኔታ በቀጥታ ስርጭት ያዩ ናይጄሪያውያን ደግሞ ለፕሮፌሰሩ ጤንንት ሲጸለዩ ታዩ፡፡
#ያሳዝናል…
የኋላ ኋላ ሲጣራልህ ፕሮፌሰሩ የሀገራቸውን ህዝብ ልብ ያንሰፈሰፈ ፌንት አነቃቀላቸው ለካ ሆነ ብለው ከተጠያቂነት ለማምለጥ ሲሉ ለሳምንታት በቤታቸው ተለማምደው የተወኑት ፕራንክ ወይም ድራማ ነበር።
ታዲያ ይሄን የሰማው የናይጄሪያ ህዝብ ምን ቢል አሪፍ ነው?
“ፕሮፍ የሀገሪቷ የትወናን ጥበብ አንድ ደረጃ ከፍ ያደረጉ በመሆናቸው ‘ኖሊውድን’ ይምሩልን¡”
#ወዳጄ
ይሄንን አላምንም ካልክ የናይጄሪያ የመድረክ ተዋንያንን ያስናቀውን የፕሮፌሰሩን ትወና ቪዲዮ Channels Television ዩቱብ ላይ Drama As NDDC MD, Pondei, 'Slumps' During Reps Cmtte' Interrogation ብለህ ተመልከተው።
:- SOLOMON TADESE AWEKE
👉ፔጃችንን ላይክ እና ፎሎው በማድርግ ቤተሰብ እንሁን!🙏
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/zumra_tube