15/10/2025
ዶ/ር ሂሩት ካሳው ዋትስአፕ አካውንት ተጠልፏል! 🚨
አዲስ አበባ – የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህል፣ የኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር) ዋትስአፕ (WhatsApp) የግል አካውንታቸው መጥለፉን (Hacked) አስታውቀዋል።
ዶ/ር ሂሩት ካሳው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ውድ ጓደኞቻቸው እና የስራ ባልደረቦቻቸው በአሁኑ ሰዓት ከእርሳቸው ዋትስአፕ አካውንት በሚመጣ ማንኛውም መልዕክት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
👉 ማስጠንቀቂያው ምን ይላል?
* ምላሽ አይስጡ! በስሜ ከሚመጣ ማንኛውም መልእክት ምላሽ መስጠት የለብዎትም።
* መልእክት አይላኩ! ምንም አይነት መልእክት ወደ ተጠለፈው አካውንት አይላኩ።
አካውንቱ ከተጠለፈ በኋላ መልእክት ወይም ጥያቄ ሊቀርብ ስለሚችል፣ ማንኛውም ሰው ጥንቃቄ እንዲያደርግ እና ለደህንነት ሲባል ምንም አይነት መረጃ ወይም ገንዘብ ነክ ጥያቄ ምላሽ እንዳይሰጥ ጥሪ ቀርቧል።
©️ዶ/ር ሂሩት ካሳው
🙏🙏🙏
🌴🌴🌴