EK Media Channel

EK Media Channel Honestly truly news and current situation

ኢኬ መረጃ ኢትዮጵያያልታደለች ሐገርየደቡብ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ ፦" በሳውላ በውሃ ሃብት ልማት ፅ/ ቤት ውስጥ የውሃ ተቋም ግንባታ እንዲደረግ ከክልሉ የተላከውን ሃብት በመ...
21/04/2022

ኢኬ መረጃ ኢትዮጵያ

ያልታደለች ሐገር

የደቡብ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ ፦

" በሳውላ በውሃ ሃብት ልማት ፅ/ ቤት ውስጥ የውሃ ተቋም ግንባታ እንዲደረግ ከክልሉ የተላከውን ሃብት በመውሰድ የፕሮጀክት ማናጀር/ የውሃ ፕሮጀክት ፅ/ቤቱ ኃላፊ የራሱን ቤተሰብ ባለቤቱንና ሌሎች አካላት በማህበር እንደተደራጁ በማድረግ ከ5 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ሃብት መዝብሮ አካባቢውን በመልቀቅ አዲስ አበባ በመግባት የግል ድርጅት በማቋቋም ሲንቀሳቀስ የፋይናንስ ኦዲተሮች በመሄድ ኦዲት በማደርግ ለፍ/ቤት ቀርቦ ኦዲቱ ተገቢ መሆኑንና ጉድለቱ በመረጋገጡ ይህን በዋናነት የሰራው አካል በ9 ዓመት እና 50 ሺህ ብር ቅጣት፤ ባለቤቱ 8 ዓመት እና ተመሳሳይ የገንዘብ ቅጣት፤ ያስተባበሩ የመሩ ፣ አጠቃላይ ለብክነቱ ተዋናይ ናቸው የተባሉ የማናጅመንት አካላት እያንዳዳቸው 5 ዓመት የጎፋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ውሳኔ እንዲያሳልፍ ተደርጓል"

" በሃዲያ ዞን በአንዳንድ ወረዳዎች ላይ ከባንክ ጋር በመመሳጠር አንድ 6,500 ደሞዝተኛ የሆነ አንድ 0 በመጨመር 65,000 ብር ደሞዝ በባንክ ሲተላለፍለት እንደነበር እንዲሁም ደግሞ 130 ሺ ብር ደሞዝ በወር የሚከፈለው ሰው በማግኘት ግለሰቦቹንም ባንኩ ውስጥም የሚያስተዳድሩት ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ገንዘቡ ተመላሽ እንዲሆን እያተሰራ ነው "

" በከምባታ ዞን ወረዳዎች ውስጥ በሌሉ ሰዎች ስም በገዛ ቤተሰብ ስም በባንክ አካውንት ደሞዝ በየወሩ የማስገባት ድርጊት በጥቆማ ተደርሶ ሰዎቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል "

" በሃላባ ዞን የፅህፈት ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስተሻል ስትባል ወዲያው ባንክ ቤት በመሄድ ወደ ግለሰብ አካውን 700 ሺ ብር እንዲዞር በማድረግ ከባንክ ለማውጣት ስትል እርምጃ በመውሰድ፣ተባባሪዎችን በማሰር ሃብቱን ወደመንግስት ካዛና እንዲመለስ ተደርጓል "

https://t.me/EKMEDchannel

የኢትዮጵያ መንግስት በሩሲያ ኤምባሲ የወጣውን መግለጫ እንደሚደግፍ አስታወቀ*************************የኢትዮጵያ መንግስት በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ ለሩሲያ ጦር ኃይል የወታደ...
20/04/2022

የኢትዮጵያ መንግስት በሩሲያ ኤምባሲ የወጣውን መግለጫ እንደሚደግፍ አስታወቀ
*************************

የኢትዮጵያ መንግስት በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ ለሩሲያ ጦር ኃይል የወታደሮች ምልመላ እየተከናወነ እንደሆነ የሚገልፁ መሰረተ ቢስ ዘገባዎችን አስመልክቶ ያወጣውን አቋም መግለጫ እንደሚደግፍ አስታወቀ።

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በ1961ዱ የቬና ኮንቬንሽን መሰረት ኤምባሲው ምንም ዓይነት ወታደራዊ ምልመላዎችን እየተቀበለ አለመሆኑን ግልፅ ማድረጉን አመላክቷል።

መሰል ወታደራዊ ምልመላዎች ከዲፕሎማሲ ስራ በተቃራኒ በመቆም የቪዬና ኮንቬንሽንን የሚጥሱ መሆናቸው ተገልጿል።

መሰል ኢትዮጵያውያንን ለወታደራዊ እንቅስቃሴ የመመልመል ተግባር በኢትዮጵያ ህግ የተከለከለ በመሆኑ ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮው የአስተናጋጅ ሀገርን ሕግ እና ደንብ እንዲያከብር የሚያስገድደውን ዓለም አቀፍ ስምምነት ጭምር የሚጥስ ነው ተብሏል።

በዚህም ኤምባሲው የወሰደውን እርምጃ የኢትዮጵያ መንግስት ያደንቃል ብሏል።

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)አዲስ አበባ ዩክሬን ኢምባሲበአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ ፥ " ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለ...
19/04/2022

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)

አዲስ አበባ ዩክሬን ኢምባሲ

በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ ፥ " ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ ነው " ፤ ኢትዮጵያውያኑ የተሰለፉት ድጋፍ ለመግለፅ ነው ማለቱ ይታወሳል።

የዩክሬን ኤምባሲ ግን ማስተባበያው እራሱ ሀሰተኛ ነው ብሏል።

ኤምባሲው ፤ " በተለያዩ የማህበረሰብ ትስስር ገጾች እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ ነው " መባሉ " በራሱ ውሸት ነው " ሲል ገልጿል።

ሩሲያ አሁን ላይ ከኢትዮጵያ ወጣቶችን ለመመልመል ሙከራ እያደረገች ትገኛለች ብሏል።

የኤምባሲው የሚሽን ሃላፊ አሌክሳንደር ለአል ዓይን በሰጡት ቃል፥ ከሰሞኑ አንድ የሩሲያን ወታደራዊ የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) የለበሰ ሰው አዲስ አበባ ገብቷል ሲሉ ተናግረዋል።

የሰውዬው መግባት ከጉዳዩ ጋር ምን እንደሚያገናኘው ተጠይቀው " ዩኒፎርም የለበሰው ወታደር መቼም በግ ጠባቂ አይደለም፣ ወታደር እንጅ " ሲሉ መልሰዋል።

ሩሲያ "70 በመቶ የሚሆነው ጦሯ አልዋጋም ስላላት ኢትዮጵያውንን ለመመልመል ጥረት እያደረገች ቢሆንም ኢትዮጵያውያን ግን ፈቃደኛ አልሆኑላትም" ሲሉም ተናግረዋል።

ሩስያ ምልመላ ለማድረግ እየሞከረች ነው ያለው የዩክሬን ኤምባሲ " የተለያዩ መደለያዎችን እሰጣለሁ " በማለት ነው ኢትዮጵያውያንን ለመመልመል ጥረት እያደረገች የምትገኘው ሲል ለአል ዓይን ኒውስ ገልጿል።

ምንም እንኳን ሩስያ " ለምልመላ ማስታወቂያ አላወጣሁም፤ እንዲህም አላደርግም " ብትልም ዛሬም ሰዎች በተለይ ዶክመትን የያዙ ወጣቶች ኤምባሲው በር ላይ ተሰልፈው እንደነበር ቢቢሲ ፅፏል።

በኤምባሲው በር ላይ ተሰልፎ የነበረ አንድ ወጣት በጥሩ ደመወዝ በወታደርነት ወይም በተገኘው ስራ ለመቀጠር እንደመጣ ተናግሮ " ሩሲያን እወዳታለሁ " ብሏል።

https://t.me/EKMEDchannel

ኢኬ መረጃ (ደቡብ አፍሪካ)ደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አገልግሎትሼርማሳሰቢያክረምቱ እየተቃረበ ነዉ ደመናማና ጭጋጋማ የአየር ሁኔታዎች ይጠበቃሉ።ጥንቃቄ ያድርጉበጭጋጋማና ደመናማ እንዲሁም በጨለማ ወቅ...
19/04/2022

ኢኬ መረጃ (ደቡብ አፍሪካ)
ደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አገልግሎት

ሼር

ማሳሰቢያ

ክረምቱ እየተቃረበ ነዉ ደመናማና ጭጋጋማ የአየር ሁኔታዎች ይጠበቃሉ።

ጥንቃቄ ያድርጉ

በጭጋጋማና ደመናማ እንዲሁም በጨለማ ወቅት ርቀት መንገድ መሄድ ግዴታዎ ሊሆን ይችላል ምን ግዜም በሚጓዙበት ወቅት አስቀድመው ጥንቃቄ ይዉሰዱ።

የሚሄዱበትን ቦታ አንድ ሰው እንዲያውቅ ያድርጉ
የቤተሰብ አባል ወይም ለታመኑ ጓደኞችዎ የት እንደሚሄዱ እና መቼ መድረስ እንዳለቦት ያሳውቁ።

የተመቸ ጫማ ይምረጡ
ከአደጋ ግዜ ለመሸሽ የሚያስችል የተመረጡ ጫማዎችን ይጠቀሚ።

ብሩህ እና የሚታይ ወይም አንጸባራቂ ልብስ ይልበሱ
መንገዶችን ሲያቋርጡ ጥንቃቄ ያድርጉ ለተሽከርካሪዎች መታየትዎን ያረጋግጡ።

በጉዞ ወቅት ሰዎች የሚበዙባቸዉን መንገዶች ይጠቀሙ ጭር ካሉ አካባቢዎችን ባይጠቀሙ ይመረጣል።

ስለሚሄዱበት አካባቢ መረጃ ይኑሮ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት አጠራጣሪ ሰዎችን ወይም መኪኖችን የማየት ዕድሉ አነስተኛ ስለሚሆን ያስተዉሉ።

የጆሮ ማዳመጫዎችን አይጠቀሙ ወይም ስልኮን ሲጠቀሙ ይጠንቀቁ ከአለአስፈላጊ ምክንያት ከስልኮ ይቆጠቡ።

ከፊት ለፊት በሚመጡ ተሽከርካሪዎች የትራፊክ አቅጣጫ ተከትለው ይራመዱ።

ሁልጊዜ ወደ እርስዎ የሚመጡትን መኪኖች ለማየት እና ተሽከርካሪዎች ከኋላዎ መከተል ወይም ለማንኛዉም አላስፈላጊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳይችሉ ከፊት ለፊቶ መኪና በሚመጣበት አቅጣጫ ይራመዱ።

አላስፈላጊ ዉድ እቃዎችን አይያዙ ከያዙም መደበቅ ይቻሉ ።

እንዳይዘነጉ አደጋ ካጋጠምዎ የፖሊስ እርዳታ ማግኘት እንዲችሉ 10111 የመደወል ፍጥነት ይኑሮ።

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አገልግሎት።

https://t.me/EKMEDchannel

19/04/2022

ኢኬ መረጃ (ደቡብ አፍሪካ)

ኩዋዙሉ ናታል

በጎርፍ አደጋ ዠተጠቃዉ የኩዋዙሉ ናታል አካባቢ ዘረፋ እየተካሄደ እንደሚገኝ አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ትናንት በኢትቀዋኒ ዱሚሳኒ መንገድ ላይ የሾፕ ራይት ሸቀጥ የጫነ ከባድ መኪና እንደዚህ ተዘርፏል።

አሳዛኝ ነዉ?

DUMISANI MKHAYA RD. INANDA. ETHEKWINI. KZN. TRUCK BEING LOOTED. POLICE RESPOND. 18/05/22

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)ሩሲያ ኣንባሲ አዲስ አበባእነዚህ ወጣቶች ከሩሲያ ጎን በመሠለፍ ከዩክሬን ጋር የሚካሄደዉን ጦርነት ለመዋጋት የተሰለፉ ናቸዉ። የሚጠብቃቸዉ እጣ ፈንታ ሞት ወይም ጠቀም ያ...
18/04/2022

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)

ሩሲያ ኣንባሲ አዲስ አበባ

እነዚህ ወጣቶች ከሩሲያ ጎን በመሠለፍ ከዩክሬን ጋር የሚካሄደዉን ጦርነት ለመዋጋት የተሰለፉ ናቸዉ።

የሚጠብቃቸዉ እጣ ፈንታ ሞት ወይም ጠቀም ያለ ገንዘብ ነዉ።

ለሐገሩ ያለምንም ክፍያ ሲሰዋ የነበረዉ ያገሬ ወጣት ድህነት አሸንፎታል።

እዉነቱ ለሩሲያ አስቦ ወይም ወግኖ አይደለም እዉነቱ እርሱ ሞቶ የሚኖርለት ቤተሰቡን በህይወት ማቆየት ነዉ።

እንደዚህ የሚያሳዝን ዘመን ገጥሞን አያዉቅም።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይጎብኛት በቃቹ ይበለን😭😭😭

ለማንኛውም ከላይ የሰራነዉ ዜናን በተመለከተ ራሺያ አስተባብላለች!

ሩሲያ ኢትዮጵያውያን ወዶ ዘማቾችን እየመለመለች ነው መባሉን አስተባበለች፡፡

ከሰሞኑ በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ መግቢያ በር ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ጭምር ተሰልፈው ታይተዋል።

የሩሲያ ኤምባሲ በር ላይ ኢትዮጵያዊያኑ ለምን ተሰለፉ ለሚለው ኤምባሲው ለአል-ዐይን አማርኛ ማብራሪያ ሰጥቷል
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ መግቢያ በር ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ለሩሲያ ዩክሬንን ለመውጋት ለመመዝገብ ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ናቸው የሚል ምስል በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
አል ዐይን አማርኛ ጉዳዩን በሚመለከት በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ጠይቋል።

የኤምባሲው ፕረስ አታቼ ማሪያ ቸርኑኪና ለአል ዐይን እንዳሉት “ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ ነው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።

ይሁንና ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት “በርካታ ኢትዮጵያዊያን በኢሜይል እና በአካል ከሩሲያ ጎን መሆናቸውን እያሳወቁን ነው ለዚህ እናመሰግናለን” ሲሉም አክለዋል።

ኢትዮጵያዊያን ይሄንን እያደረጉ ያለው ረጅም እና ታሪካዊ በሆነው የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ወዳጅነት ላይ ስለሚተማመኑ እንደሆነም ኤምባሲው ተገልጿል።

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦርን ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ሩሲያ እና ዩክሬን ይፋዊ ጦርነት ከጀመሩ 54ኛ ቀኑን ይዟል።

https://t.me/EKMEDchannel

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)ሸዋሮቢት በሸዋሮቢት እና አካባቢው ዳግም ግጭት አገርሽቷል።በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ኦሮሞ ብሄረሰብ አዋሳኝ አካባቢዎች ትናንት 10፡30 ዳግም ግጭት አገርሽቷል።ግጭ...
18/04/2022

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)

ሸዋሮቢት

በሸዋሮቢት እና አካባቢው ዳግም ግጭት አገርሽቷል።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ኦሮሞ ብሄረሰብ አዋሳኝ አካባቢዎች ትናንት 10፡30 ዳግም ግጭት አገርሽቷል።

ግጭቱ የተከሰተው ከሸዋ ሮቢት ወደ ደሴ በሚወስደዉ አዋሳኝ ጀጋኖ፣ ጀጀባ ፤ሞላሌ እና መቃ አካባቢዎች ነው የተከሰተው።

እስካሁን ባለው መረጃ አንድ ፖሊስ ሲሞት በርካቶች ደግሞ ቆስለው ወደ ህክምና ቦታዎች ተወስደዋል።

መንስኤው በመሬት እንደሆነ ነው እየተነገረ ያለዉ።

መንግስት በአፋጣኝ ጣልቃ ካልገባ ይህን መሠሉ ጥቃት ወደ አደገኛ ዉጊያ ሊቀየር የሚችልበት ሁኔታ ሰፊ ነዉ።

https://t.me/EKMEDchannel

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ) ____ሼር ሼር ሼር___በኦሮምያ ክልል ንብረታቸዉ በሙሉ የወደመባቸዉ ግለሰብ ለኢኬ ሚዲያ ቻናል የላኩት መልእክት ነዊ።😭 ይድረስ ለሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር!😭 ይድረስ...
16/04/2022

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ) ____ሼር ሼር ሼር___

በኦሮምያ ክልል ንብረታቸዉ በሙሉ የወደመባቸዉ ግለሰብ ለኢኬ ሚዲያ ቻናል የላኩት መልእክት ነዊ።

😭 ይድረስ ለሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር!

😭 ይድረስ ለክብር ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት !

😭- ይድረስ ለኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት -

😭 ይድረስ የኢትዮጵያ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት -

ይድረስ ለዝዋይ ባቱ ርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት -

ይድረስ ለዝዋይ ባቱ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

ይድረስ ለኦሮምያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት

ይድረስ ለኦሮምያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት -

ይድረስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት -

ይድረስ ለዳሽን ባንክ ዋና ቢሮ አዲስ አበባ ለዳሽን ባንክ ሀዋሳ እና ዝዋይ ባቱ -

ጉዳዩ - የህግ የበላይነት እንዳከበር እና የመልካም አስተዳደር በደልና ግፍ በአግባቡ እንዲፈታ ስለመጠየቅ ይሆናል -

ይህን የምታዩት ጽሁፍ የፃፍኩት እኔ እያሱ ሻንቅሎ እባላለሁ በ2010 ዓ ም በኦሮሚያ ክልል በዝዋይ ባቱ ከተማ ሀብትና ንብረቴን በጠራራ ፀሐይ ወድሞ እያለ ፍትህ የሚሰጠኝ የመንግስት አካል በማጣቴ በደል ደርሶብኛል።

ስለዚህ ይህን ጽሁፍ አይቶ ፈጣን ምላሽ እና ፍትህ እንዲሠጠኝ በእግዚአብሔር ስም
እጠይቃለሁ።

ኢትዮጵያ ትቅደም ብልፅግና ይረጋገጥ።

ለበለጠ መረጃ - 👇👇👇

09 12 40 00 31 / 09 11 71 47 84

https://t.me/EKMEDchannel

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)ሐይቅ ከተማ ሀይቅ ከተማ ከፍተኛ የውሃ እጥረት ተከስቷል። በጦርነት ሰንብታ የነበረችዉ ሀይቅ ከተማ የዉሀ እጥረት ተከስቷል ህዝቡ የመጠጥ ዉሃ ለማግኘት ከባድ የሚባል ሁ...
16/04/2022

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)

ሐይቅ ከተማ

ሀይቅ ከተማ ከፍተኛ የውሃ እጥረት ተከስቷል።

በጦርነት ሰንብታ የነበረችዉ ሀይቅ ከተማ የዉሀ እጥረት ተከስቷል ህዝቡ የመጠጥ ዉሃ ለማግኘት ከባድ የሚባል ሁኔታ እየተጋፈጠ ይገኛል።

መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ ቢወስድ ይመረጣል።

https://t.me/EKMEDchannel

ወደ ሐገር ቤት ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሀገር ቤት ጉዞን ተከትሎ የተዘጋጁ መርሀ ግብሮችን ይፋ ማደረጋቸወው ይታወሳል። በመርሀ ግብሮቹ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ከሆነ አስቀድው በቀላሉ መመዝገብ የ...
16/04/2022

ወደ ሐገር ቤት

ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሀገር ቤት ጉዞን ተከትሎ የተዘጋጁ መርሀ ግብሮችን ይፋ ማደረጋቸወው ይታወሳል።

በመርሀ ግብሮቹ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ከሆነ አስቀድው በቀላሉ መመዝገብ የሚያስችልዎ ሊንክ በኢትየጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ይፋ ተደርጓል፡፡

በመሆኑም ኤምባሲው በአገራዊው ጥሪ ላይ እንድትሳተፉ በታላቅ አክብሮት ለማስታወስ ይወዳል፡፡

እንዲሁም ከዚህ በታች የቀረበውን ሊንክ በመጫን ወይም በኤምባሲው ዘንድ በቀጥታ በመደወል መሳተፍ ለምትፈጓቸውን ሁነቶች እንዲመዘገቡ የተጋበዛችሁ መሆኑን እያሳወቅን፤ ለተጨማሪ መረጃ +27727154957 (WhatsApp) በመደወል በቀላሉ ማግኘትና መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃልን፡፡

ኢኬ መረጃ (ደቡብ አፍሪካ)ደርባንከደርባን ንግድ ምክር ቤት፡-(SASSA)የምግብ እና የመጠጥ አቅርቦቶችን ለመለገስ እና በደርባን በጎርፍ ለተጎዱ አካላት እርዳታ ለመስጠት ለምትፈልጉ ሁሉ ከደ...
16/04/2022

ኢኬ መረጃ (ደቡብ አፍሪካ)

ደርባን

ከደርባን ንግድ ምክር ቤት፡-(SASSA)

የምግብ እና የመጠጥ አቅርቦቶችን ለመለገስ እና በደርባን በጎርፍ ለተጎዱ አካላት እርዳታ ለመስጠት ለምትፈልጉ ሁሉ ከደርባን መንግስታዊ አካላት ጋር ይገናኙ።

በፍጥነት ደራሽ ለመሆን የሚከተለውን የ SASSA ሲኒየር አስተዳደሮች ያነጋግሩ።👇👇👇

From Durban Chamber of Commerce:

For immediate interventions please contact the following SASSA Senior Management.

Ethekwini and Ilembe District
Please contact 0843800007 Ms Jay Naicker

Umzinyathi, Uthukela and Amajuba Districts
Please contact 0724091377 Mr Sekela Zulu

Umgungundlovu, Ugu and Harry Gwala Districts
0722005420 Mr Mlungisi Mdima

Zululand, King Cetshwayo and Umkhanyakude Districts
0835210107 Mr Khanyisani Mbatha

Provincially
Contact Ms Winnie Mofokeng
+27635095580

Mr Vusi Mvubu
0835770969

Kind regards
Dennis Hlengwa SASSA

https://t.me/EKMEDchannel

15/04/2022

ኢኬ መረጃ (ኢትዮጵያ)

, 📍

ትላንትና በጉዞ ላይ እንደነበሩ የተነገረላቸው አስፈላጊ የሆኑ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶችን የጫኑት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ተሸከርካሪዎች የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ደርሰዋል።

ሁሉም (50ውም) ተሸከርካሪዎች በሰላም ነው መቐለ የደረሱት።

ምን ይዘዋል ?

➡️ 1,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴ እና ጥራጥሬ ፤
➡️ 700 ሜትሪክ ቶን የጤና ፣ የተመጣጠነ ምግብ እና WASH (ውሃ፣ የአካባቢ እና የግል ንፅህና መጠበቂያ እቃዎች) + 115,000 ሊትር ነዳጅ ይዘው ነው መቐለ የደረሱት።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም መቐለ የደረሱትን እነዚህን ምግብ / አልሚ ምግቦች በዚህ ሳምንት በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ማከፋፈል እንደሚጀምር አሳውቋል።

በዚህም ድርጅቱ 43,000 አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች እንዲሁም ተጋላጭ ለሆኑ 24,000 እናቶች እና ህጻናት በተመጣጠነ ምግብ ለመድረስ ማቀዱን ገልጾል።

https://t.me/EKMEDchannel

Address

Johannesburg

Telephone

+27720565941

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EK Media Channel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share