የኛ ሰው ከደቡብ አፍሪካ

የኛ ሰው ከደቡብ አፍሪካ ትኩስ መረጃዎችን ለማግኝት like and share ያድርጉ ።

ለትግራይ ህዝብ ማነው የሚጠቅመው ?
04/04/2025

ለትግራይ ህዝብ ማነው የሚጠቅመው ?

14/03/2025

ዳግማዊ መንግሥቱ ኃይለማርያም የሆነው አቢይ አሕመድ በኤርትራ ላይ ጦርነት ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የአደባባይ ሃቅ ነው። እውነት ለመናገር [የግዴታ] ካልሆነ በስተቀር የኤርትራ መንግሥት ከአቢይ ጋር ለመዋጋት ፍላጎት የለውም። ነገር ግን፥ አቢይ ወረራ እስከፈፀመበት ድረስ "አማራጭ" ስለሌለው ራሱን ለመከላከል ይዋጋል። የኤርትራ መንግሥት የሚዋጋው ግን ብቻውን አይደለም።

የኤርትራ መንግሥት አቢይ አሕመድ የቃጣበትን ወረራ ለመመከት የግዴታ ብቻውን ሳይሆን በራሱ አቢይ ላይ ያኮረፈውን የሕወሓት ታጣቂ ክንፍ ይዞ ነው። ይኼ [የኤርትራ መንግሥትና የወያኔ ጥምረት] ጊዜያዊም ቢሆን ለኢሳያስ አማራጭ ስለሌለው እንደ plan B ተጠቅሞ መዋጋቱ አይቀሬ ነው።

እዚህ የኃይል አሰላለፍ ላይ ግን ማለትም አቢይ አሕመድ ከኢሳያስና ደብረጽዮን ጥምረት ጋር ሲገጥሙ ውጤቱ እንዲህ በቀላሉ የሚገመት አይደለም። ምናልባትም የኃይል መመጣጠን ስለሚኖር ቶሎ አሸናፊ ላይኖር ይችላል። ከየራሳቸው አቢይና ኢሳያስ (ደብረጽዮን) ባሻገር የአረቡ ክፍልም በተዘዋዋሪ በሁለቱ ሐገሮች ጎራ ተሰልፎ እንደሚያዋጋ ሐቅ ነው። ሳዑዲዓረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች፣ ቃጣር፣ ግብፅና መሰል ሌሎች ፀረ-ኢትዮጵያ ሐገራት ይሳተፉበታል።

በእኔ አተያይ አቢይ ጦርነቱን ቢፈልገውም የኢሳያስ-ደብረጽዮን ጥምረት ወታደራዊ አሰላለፍ የኃይል ሚዛን ስለሚቀይር ምናልባትም ጦርነቱ የማይደረግበት አጋጣሚ ሊኖር ይችላል። አቢይ [በአሰብ] ጉዳይ ከኤርትራ ጋር ሊዋጋ የነበረውን አጀንዳ ለጊዜው አጥፎ ቅድሚያ ወያኔን ለማጥፋት ሊዋጋ ይችል ይሆናል። ግን ደግሞ "ከወያኔ መጥፋት በኋላ አማራውስ" የሚለው ጥያቄ እንደሚመጣበት ሃቅ ነው። ምክንያቱም የኦሮሞ ኃይል በአማራ ጉዳይ የስልጣን ማስጠበቂያው ወያኔ ነው። [እንበልና] ወያኔን ገሸሽ ካደረገ በኋላ ቀጥሎ ወደ ኤርትራ መሄዱ አይቀሬ ነው። ነገር ግን [ነቄው] ኢሳያስ አፈወርቂ የአቢይን አካሄድ ስለሚያውቅ ቀድሞ ወያኔ survive እንዲያደርግ ሊረዳው ይችላል። ምክንያቱም ወያኔን ከጨረሰ በኋላ ወደ ኤርትራ እንደሚሄድ ስለሚያውቅ።

ሌላው ደግሞ፥ ምናልባትም አቢይ ወያኔ ላይ ጦርነት ቢከፍት ጦርነቱ ከመጠናቀቁ በፊት ኢሳያስ የአሰብ ወደብን ቀድሞ ለአረቦች ሊያከራየው ይችላል።

የአሰብ ወደብ ጥያቄ እና የፕሪቶሪያ ስምምነት ወደ ጦርነት ወይስ እፎይታ?============•••••••===============ህወሃት የፕሪቶሪያ ስምምነት ላይ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ነጥብ...
11/03/2025

የአሰብ ወደብ ጥያቄ እና የፕሪቶሪያ ስምምነት ወደ ጦርነት ወይስ እፎይታ?
============•••••••===============
ህወሃት የፕሪቶሪያ ስምምነት ላይ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ነጥብ ሰጥታ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር አጣላችው። ዶ/ር አብይ ከጦርነት እፎይታ እና ለተወሰኑት ስልጣን ሰጥቶ እና ዶ/ር ደብረጽዮንን ከስልጣን አስነስቶ እርስ በርስ አጣላቸው። አሁን ገሚስ ህወሃት ከዶ/ር አብይ ሌላው ከኢሳያስ ጋር አብሯል።

ይህ የፖለቲካ ክላሽ የፈጠረው ስንጥቅ እና ፖላሪዜሽን ፓርቲአዊው እና መንግስታዊው ህወሃት ታርቀው ኢሱ እና አብይም ታርቀው ሊያልቅ የሚችልበት scenario probability zero የሚባል አይደለም። ነገር ግን ideal scenario ተደርጎ ሊታይ የሚችል እና ሁላችንም የምንመኘው እና ቢፈጠር ደስ የሚለን አጋጣሚ ነው። ነገር ግን በምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካ ውስብስብነት አይን ሲታይ ኔይቭ መሆን ነው ያስብላል።

ሁለተኛው ፓርቲአዊው ህወሃት [በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው] ከኢሳያስ ጋር አብሮ ትግራይን ለአስተዳደር የማትመች ከማድረጉ mild aggression ከጨከነ መንግስት ግልበጣ [ትግራይ ላይ ጀምሮ እዛው የሚያቆም እና የመሃል ሃገርን ፖለቲካ የሚያናጋ ወይም ከባሰ እና ከቻለበት መንግሥት ግልበጣ የሚከጅሉትን ማገዝ እና ምናልባትም ማስቻል] ሊፈፅም የሚችል ሲሆን ይህ ጦርነትንም ከማካተት የማይመለስ ተደርጎ ሊታይ ይችላል።

ሶስተኛው መንግስታዊው ህወሃት [በትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራው ሲሆን መዋቅር እና ፋይናንስ የሚቆጣጠር በዋነኝነት በወጣቶች የሚደገፈው ቡድን የፓርቲአዊውን ህወሃት አባላት ከማሰር አነስተኛው እርምጃ አንስቶ ከመሃል ሃገር መንግስት ጋር በማበር] በኢሳያስ ላይ ጦርነት ሊጀምር በአሥመራ የመንግስት ለውጥ ሳይፈጥር የማይመለስ እርምጃ ሊወስድ የሚችልበት አጋጣሚ አለ።

ይህ እንግዲህ በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ጉዳይ እጁን አስገብቷል የተባለው የአስመራው መንግስት የሚያስታጥቀው ፋኖ የሚያነሳው የወልቃይት [ፀ/ጠ]ገዴ እና በመሃል ሃገር ህወሃት ከመጣ ይቀማኛል ብሎ የሚያስበው የማዕከላዊ ፖለቲካ ድርሻ ጉዳይ [የድሮ ክስተቶች ነቆራ ለዚህ መንደርደሪያ ነው] ዋናው መነሻ ሲሆን ከቆየ ቂም አንፃር የአሰብን ወደብ ጥያቄም እንደ ህዝብ ማስተባበሪያ ይዞት ይነሳል። ይህ ማለት የማያባራ እልቂት ከማስከተሉ ማግስት ምናልባት በአስመራ የማይቀር የሚመስል በኢትዮጵያም ሊከሰት ዕድል ያለው የመንግስት ለውጥ ሊፈጥር ይችላል።

በዚህ ሁሉ ግን ህወሃት ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦርነት የምታገኘው የሚሊተሪ እና ፖሊቲካል ስትራቴጂክ ትርፍ በስመ ሰላም በረዥም ጊዜ ከሚገድለው በማደንዘዣ እያለሳለሰ ሽልብ ከሚያደርግ ሞት ይልቅ ለመብት በትጥቅ መታገልን እና የሚሞተው ሞቶ የተረፈው መብቱ በትክክል ተጠብቆ እና ተከብሮ ይኑር ብላ ከወሰነች ጦርነት የማይቀር እና ጊዜን ብቻ የሚጠብቅ የዘመናችን ታሪክ አጋጣሚ ይሆናል ማለት ይቻላል።

ይህ ማለት አብይም ኢሳያስም ዶ/ር ደብረጽዮንም ጌታቸው ረዳም በተናጠልም ሆነ በግል ጉዳዩን ወደ ጦርነት የማስገባት ሚና ሊጫወቱ የሚችሉበት ዕድል [ምን ዕድል ይባላል አማርኛው እጅ አጥሮት probability ለማለት ሆነ እንጂ ይህ ነፍሰ በላው የዕድል ጎዶሎ] አለ።

ስለዚህ አንድ ሌሊት በትግራይ ክልል ወይም በኢትዮጵያ እና በኤርትራ [መንግስታት] መካከል ጦርነት ተቀሰቀሰ የሚል ሰበር ዜና ሊከሸከሽልንም ይችላል።

በተቃራኒው አራቱም ካምፖች የኦሮማራውን ፋኖአይዝድ የአማራ ብልፅግና ጨምሮ በአምስት ዝሆኖች መስማማት ለቀጣይ ሃያ አምስት አመታት በአፍሪካ ደረጃ የተረጋጋ የሚባል ምስራቅ አፍሪካን ወደ ሰላም መረጋጋት እና ተባብሮ ማደግ ሊያሸጋግር የሚችልበትም ዕድል አለ።

እዚህ ውስጥ ደቡብ ግን ሚናው ምንድነው? አለ?

ቸር ያሰማን!

11/03/2025

የዚህ ክልል ልዩ ሀይል እያልክ ገዳይ ከምታበዛ፤የዚህ ክልል አምራች ሀይል ብለህ ፖሊሲህን አሻሽል!

ነዳጅ አወጣን ፥ መንኮራኩር አመጠቅን ፥ ዝናብ አዘነብን ፥ ስንዴን Export አደረግን ፥ የወደብ ባለቤት ሆንን፥ድሮን አመረትን.......SHORT ሚሞርያም ሁላ አጃኢብ ነው።አያልቅበት!!!
10/03/2025

ነዳጅ አወጣን ፥ መንኮራኩር አመጠቅን ፥ ዝናብ አዘነብን ፥ ስንዴን Export አደረግን ፥ የወደብ ባለቤት ሆንን፥ድሮን አመረትን.......SHORT ሚሞርያም ሁላ አጃኢብ ነው።አያልቅበት!!!

በየመድረኩ የህዝብን ጥያቄ ሲቻል እየደፈጠጡ ሳይሆን ሲቀር እየሸፋፈኑ ማለፍ የእራስ ወዳድነትና አልጠግብ ባይ  ወንበር አፍቃሪነት ነው ":: ቂምና ጥላቻ እጅግ የከፉ ሰብዓዊ አራጣዎች ናቸው፡...
05/03/2025

በየመድረኩ የህዝብን ጥያቄ ሲቻል እየደፈጠጡ ሳይሆን ሲቀር እየሸፋፈኑ ማለፍ የእራስ ወዳድነትና አልጠግብ ባይ ወንበር አፍቃሪነት ነው "::

ቂምና ጥላቻ እጅግ የከፉ ሰብዓዊ አራጣዎች ናቸው፡፡ ሲመለሱ ከነወለዳቸው ነውና፡፡ ትናንሽ ልቦች የጥላቻና የቂም ስራ ቤት ናቸው፡፡ ትላልቅ ልቦች ግን የርህራሄ ምሰሶ እና የጀግንነት ጎራ ናቸው፡"

"ሆድ ክፉ ነው። ከክብር ከፍታ ላይ ነቅሎ እና በከርስ ዝቅታ ላይ ተክሎ ብቻ አይተውህም። ራስህን ከነጻነት አምድ ላይ ቀርፈህ ከባርነት አመድ ላይ እንድታርመጠምጥም ያስገድድሀል።"

"የሞራል ምሰሶ በወደቀበት ህሊና፣ የዝርፊያ ሀውልት ይቆማል።"
በላይ ነኝ ዶቢ ክስታኔ

04/03/2025

የጉራጌ አመራሮች በሌሎች እንዳይገፉ ወይም የሌሎች መጫወቻ እንዳይሆኑ ከፈለጉ ከህዝባቸው ጎን ይሰለፉ። የወጡበት ማህበረሰብ እና የሚወክሉት ሕዝብ በዙርያቸው ያሰባስቡ። አንድ ሊገነዘቡት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር ምንም ያህል እውቀት እና ልምድ ቢኖራችሁ ጠንካራ constituency ሳይኖርህ ወይም ሳትፈጥር ከፍተኛ የስልጣን ደረጃ ላይ ብትወጣ የመንግስት ስልጣን በዋናነት ለተቆናጠጡት መሳሪያ ሆኖ ከማገልገል ውጭ የምትወክለው ሕዝብ መብትና ጥቅም ለማስከበር ልትሰራ አትችልም። ይልቁንም የሕዝብ ውግና ያሳየህ ቀን ከስልጣን ትወገዳለህ። ይህ እንዳይሆን ግን አስቀድመህ የቤት ስራህን ከሕዝብህ ጋር ሆነህ ልትሰራ ይገባል።

04/03/2025

የቀይ ባህር ጫወታ የመጣው የወታደር እጥረት ስላጋጠመው መሆኑ ተረጋግጧል! በባህር በር ሰበብ ህዝቡን አነሳስቶ በኢትዮጵያዊያን ላይ ሊያዘምትና ሊጨፈጭፍ! አይሆንም ልንለው ይገባል

Breaking! ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለዩክሬን የሚሰጠውን የአሜሪካ ወታደራዊ እርዳታ አገዱፕሬዚዳንቱ እርዳታው እንዲቆም ማዘዛቸውን ተከትሎ፣ በኦባማ አስተዳደር የዩናይትድ ስቴትስ ብሄራዊ የጸጥታ...
04/03/2025

Breaking!
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለዩክሬን የሚሰጠውን የአሜሪካ ወታደራዊ እርዳታ አገዱ
ፕሬዚዳንቱ እርዳታው እንዲቆም ማዘዛቸውን ተከትሎ፣ በኦባማ አስተዳደር የዩናይትድ ስቴትስ ብሄራዊ የጸጥታ ምክር ቤት ዳይሬክተር የነበሩት ቻርለስ ኩፕቻን "አሁን [በትራምፕ አስተዳደር] እያየነው ያለነው በግዳጅ ዲፕሎማሲ በድፍረት እጅ ጥምዘዛ ነው።" ሲሉ ለቢቢሲ ተናገረዋል::
"በመሰረቱ ትራምፕ ዩክሬናውያንን 'የአሜሪካን ጦር ትፈልጋላችሁ፣ የአሜሪካን ድጋፍ ትፈልጋላችሁ፣' ስለዚህም ከሩሲያ ጋር ወደ ድርድር ጠረጴዛ የምትሄዱበት ጊዜ አሁን ነው" በማለት በማስገደድ ዲፕሎማሲ የዩክሬንን እጅ እየጠመዘዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ለጉራጌ ህዝቦች መብት መከበር ስትሉ ብዙ እንግልትና መጉላላት አሳልፋችሁ በመፈታታችሁ ደስ ብሎናል።የጉራጌ ሕዝብ ነፃ አውጪዎች ናችሁ ፣ኮርተንባችኃል
03/03/2025

ለጉራጌ ህዝቦች መብት መከበር ስትሉ ብዙ እንግልትና መጉላላት አሳልፋችሁ በመፈታታችሁ ደስ ብሎናል።
የጉራጌ ሕዝብ ነፃ አውጪዎች ናችሁ ፣ኮርተንባችኃል

የዋና ጽ/ቤት አድራሻ ለውጥየፓርቲያችን ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ዋና ጽ/ቤት ቀድሞ ከነበረበት አራዳ ክፍለ ከተማ ወደ ልደታ ክፍለ ከተማ ባልቻ ሆስፒታል አጠገብ ወደ ሚገኘው ዳማ ህንፃ...
01/03/2025

የዋና ጽ/ቤት አድራሻ ለውጥ

የፓርቲያችን ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ዋና ጽ/ቤት ቀድሞ ከነበረበት አራዳ ክፍለ ከተማ ወደ ልደታ ክፍለ ከተማ ባልቻ ሆስፒታል አጠገብ ወደ ሚገኘው ዳማ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 405 መዛወሩን በአክብሮት እናሳውቃለን።

ጎጎት የአንድነታችን መቋጠሪያ!

በሁለቱ ሰዎች መሀከል የእውቀትም ሆነ የክህሎት ልዩነት የለም፡፡እንዲያውም ከትራምፕ ይልቅ ዘለንስኪ የተሻለ ጭንቅላት ሳይኖረው አይቀርም፡፡ነገር ግን ትራምፕ የጉልበተኛ እና ሀብታም ሀገር መሪ...
01/03/2025

በሁለቱ ሰዎች መሀከል የእውቀትም ሆነ የክህሎት ልዩነት የለም፡፡እንዲያውም ከትራምፕ ይልቅ ዘለንስኪ የተሻለ ጭንቅላት ሳይኖረው አይቀርም፡፡ነገር ግን ትራምፕ የጉልበተኛ እና ሀብታም ሀገር መሪ ነው፡፡ስለዚህ የመጮህ ፥ የመሳደብ እና የማንጓጠጥ መብቱ የሱ ነው፡፡this is how the world works.
እኛም ጥቅም አልባውን የብሄር ፖለቲካ ጥለን እከካችንን ለማራገፍ እና ከድህነት ለማምለጥ ወጥረን ካልሰራን እንዲህ ነው የሚያበሻቅጡን፡፡
በእርግጥ አሁንም በነፍሳችን እየተጫወቱ ነው!!

ለመበሻቀጥም አቅም ይጠይቃል ..መበሻቀጥ ላይ ለመድረስ ብዙ ይቀረናል

Address

Marshallstown

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኛ ሰው ከደቡብ አፍሪካ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share