Selaam tv group

Selaam tv group Serving all Ethiopian

ማንም የማንንም ኃይማኖት የማንቋሸሽና የመዝለፍ መብት የለውም። ይሄ ሁሉንም ኃይማኖቶች የሚመለከት ነው።  አንድ ተሳዳቢ የ'ርሱ ያልሆነን እምነት ሲያንቋሽሽ ስንሰማ መገሰጽ እና እንዲያርፍ ማ...
11/03/2025

ማንም የማንንም ኃይማኖት የማንቋሸሽና የመዝለፍ መብት የለውም። ይሄ ሁሉንም ኃይማኖቶች የሚመለከት ነው። አንድ ተሳዳቢ የ'ርሱ ያልሆነን እምነት ሲያንቋሽሽ ስንሰማ መገሰጽ እና እንዲያርፍ ማሳሰብ እንጂ ማዳመቅ እና ማዳነቅ ከየትኛውም ኃይማኖት አስተምህሮ ያፈነገጠ ነው።

ከዚህ ቀደም የኦርቶዶክስ ኃይማኖትን እና ተከታዮችን ሲያንቋሽሹ የነበሩ 'ተራ' ግለሰቦች ገስጸናል፤ አልገራ ሲሉም ለሕግ እንዲቀርቡ ጮኸናል፤ ወደፊትም የምናደርገው ነው።

ይሄ ሰለሞን ሽፈራው የተባለ ግለሰብ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ.) በነው^ረኛ ቃላት ሲያንጓጥጥ ዝም መባሉ እንዳለ ሆኖ ጭራሽ ጥብቅና የሚቆሙለት መኖራቸውን ማየት ያማል። ይሄ ነው^ረኛ ግለሰብ ለሕግ እንዲቀርብ መተባበርና እንደ'ርሱ ያሉ ሥርዓት አልበኞች ጥፋት እንዳይደግሙ መማሪያ እንዲሆኑ ነበር መትጋት ያለብን። እንዴት ሆኖ ነው በጥቂት ጋጠ-ወጦች ምክንያት እንዲህ ለመባባል የደረስነው?

ይህ ግለሰብ በእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ሊታለፍ የማይገባ ድንበር አልፏል፤ አልፏል ብቻ ሳይሆን በአስጸያፊ ሁኔታ በነብያችን (ሰ.0.ወ.) ተሳልቋል። እናም ለፍርድ ቀርቦ ቅጣቱን ማግኘት አለበት። ለዚህም ጥረት እያደረጉ ካሉ ወንድም እህቶቼ ጎን መቆሜን እና የሚጠበቅብኝ ለማድረግ ዝግጁ መሆኔን ለማሳወቅ እወዳለሁ። ክርስትያን ወንድም እህቶችም ለተገቢ ፍትህ ከጎናችን እንደሚቆሙ በጽኑ አምናለሁ።

11/03/2025

ሰበር ዜና

አህለሱና(ሱፍያ) ሙስሊሙን ያገለለዉ የመጅሊስ ምርጫ አካታች ሆኖ እንዲስተካከል በኦሮሚያ የተቋቋመዉ አቤቱታ አቅራቢ ግብረሀይል በደብዳቤ ጠየቀ

በኦሮሚያ የተቋቋመዉ ግበረሀይል በመጅሊሱ የሚካሄደዉ የጨረባ ምርጫ በዚህ ከቀጠለ መጅሊሱ በህገወጥነቱ ይቀጥላል ሲል ለተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ባስገባዉ ደብዳቤ ገልጿል ።

በኦሮሚያ የተቋቋመዉ ግበረሀይል በመጅሊሱ የሚካሄደዉ የጨረባ ምርጫ ያለ ተወዳዳሪና ተገዳዳሪ በአንድ ሜዳ ለብቻዉ ተወዳድሮ አሸነፍኩ ለማለት እያደረገዉ ያለዉ እንቅስቃሴ በዚህ ከቀጠለ መጅሊሱ በህገወጥነቱ ይቀጥላል ሲል ለተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ባስገባዉ ደብዳቤ ገለፀ ።

ግብረሀይሉ ይህንን ደብዳቤ ለመንግሥት መስሪያ ቤቶች ለመፃፍ ያስገደደዉ ማህበረሰቡን ያላሳተፈ የምርጫ ቦርድ በመጅሊሱ ሰያሚነት እየተቋቋመ መሆኑ መጅሊሱ ለምርጫ ዝግጁ እንዳልሆነ ማሣያ ስለሆነ ነዉ ብሏል ።

ለአብነትም በኦሮሚያ የሚገኘዉ መጅሊሱ አቋቁሜዋለሁ ባለዉ የምርጫ አስመራጭ ኮሚቴ አንድም ገለልተኛ ሰዉ የሌለበት መሆኑ ገልፆ የራሱን ጀሌዎች አመራሮች የሰበሰበበት ሂደት ስናይ ለምርጫ ዝግጁ አይደሉም ብሏል ።

ይህ ማይስተካከል ከሆነ በቀጣይ መጅሊሱ ግዜዉ ስለሚያልቅ ህገወጥ ሆኖ ይቀጥላል ካለ በሗላ የመሻኢኾቹ መጅሊስ እናቋቁማለን ።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ኢትዮጵያን ወክለው በባህሬን የዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ኮንፈረስ እየተሳተፉ ነው።ነጃሺ ቲቪ የካቲት 12/2017የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕ...
19/02/2025

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ኢትዮጵያን ወክለው በባህሬን የዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ኮንፈረስ እየተሳተፉ ነው።

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 12/2017

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ኢትዮጵያን ወክለው በባህሬን እየተካሄደ ባለው የዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ኮንፈረስ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

በባህሬን በሚከናወነው የዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ኮንፈረስ ላይ የመከፍቻ ንግግር ያደረጉት የባህሬን ንጉሥ ሀመት ኢሳ አል-ኸሊፋ ተወካይ የእንኳን የእንኳን ደህና መጣቹህ ምኞታቸውን ገልጸው በሙስሊሞች አንድነት ዙሪያ አስፈላጊነት ዙሪያ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በባህሬን የዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ጉባኤ ላይ ከተለያዩ ሀገራት የተወከሉ ዓሊሞች የታደሙበት ሲሆን በሙስሊሞች አንድነት አስፈላጊነት ዙሪያ ትኩረት ያደረጉ የጥናት ውጤቶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ተገልጿል

16/02/2025
16/02/2025

የጁሃንስበርግ ሙስሊም ሴቶች ለሰደቃ የመተባበር ጥሪ ጀመዓ ለሶስተኛ ጊዜ ልዩ ፌስቲቫል ያካሂዳል!

በብሪ ሜዳ ፌብውራሪ 15 እና 16 ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚካሄደው ይህ ደማቅ ፌስቲቫል እንዳያመልጥዎ!

በጁሃንስበርግና አካባቢው የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ሴቶች ሁሉ በዚህ ልዮ ፌስቲቫል ላይ በንቂስ ወጥታችሁ በመሳተፍ ገንዘብና ጊዜያችሁን ለመልካም ተግባር በማዋል ለአኺራ ስንቅ እንድትይዙ ተጋብዛችኋል።

የዘንድሮው ፌስቲቫል ከኢትዩጵያ የተጋበዙ እውቅ ዳዒያንና ኡስታዞች በአካል ተገኝተው የሙሃደራና ዳዕዋ ዝግጅቶቻቸውን የሚያቀርቡበት በመሆኑ ይለያል።

ይህ ልዩ ፌስቲቫል በጁሃንስበርግና አካባቢው የሚገኙ ሙስሊም እህቶቻችንን የእርስ በርስ ትውውቅ የሚያደርጉበትና አንድነታቸውን ለማጠናከር ምቹ ከመሆኑም በላይ ፈ
ለህፃናትና ታዳጊዎች ልዮ መቀራረብን ይፈጥራል።

በፌስቲቫሉ ኡስታዝ ሳዲቅ መሐመድ /አቡሃይደር/ ኡስታዝ ማህሙድ ሐሰንና ኡስታዝ ኢብሳ ሐሰን በአማርኛና ኦሮምኛ ቋንቋዎች የዳዕዋ ፕሮግራሞቻቸውን ያቀርባሉ።

የቂርአትና ቲለዋ ውድድሮችም በፌስቲቫሉ ተካተዋል።
ምን ይሄ ብቻ
በዚህ ድንቅ ፌስቲቫል ለህፃናትና ታዳጊዎች ልዮ ልዮ የመዝናኛና የጨዋታ ቦታዎች ተዘጋጅተዋል
የእግር ኳስ ውድድሮችም ይካሄዳሉ፤

ጣፋጭ ምግብና መጠጦችን እየተጠቀሙ፥ ለረመዷን ልዩ ግብይት የሚያካሂዱበት ምቹ የግብይት መድረኮችም ተፈጥረዋል።

ፌቡውራሪ 15 እና16 መንገዶች ሁሉ ወደ ቡሪ ሜዳ ያመራሉ!
ፌስቲቫሉ እየተዝናኑ የሚማሩበትና ልጆችዎ ልዮ ደስታን የሚፈጥሩበት ምቹ አጋጣሚ በመሆኑ በጁሃንስበርግና አካባቢው የምትገኙ ሙስሊም እህቶቻችን ሁሉ እንዳያመልጣችሁ የሚለው
የጁሃንስበርግ ሙስሊም ሴቶች ለሰደቃ የመተባበር ጥሪ ጀመዓ ነው!!

በኡስታዞቻችን የሙሃደራ ፕሮግራሞች መንፈስዎን አድሰው መጭውን የታላቁን ረመዷን ወር ይቀበሉ!

በዚህ አጋጣሚ ይህ ሶስተኛ ዓመት የጁሃንስበርግ ሙስሊም ሴቶች ለሰደቃ የመተባበር ጀመአ ታሪካዊ ፌስቲቫል እንዲሳካ ከሃሳብ ጀምሮ መሪ ሚናቸውን በላቀ ደረጃ ለተወጡ ሁሉ የንጃሺ ኢስላሚክ ትረስት አመራሮች ምስጋናቸውን እያቀረቡ በነገውም ፕሮግራም ሙስሊሙ ማህበረሰብ በነቂስ በመውጣት ከጎናቸው እንድንቆም ጥሪያቸውን አቅርበዋል ።

አዘጋጅ፤የጁሃንስበርግ ሙስሊም ሴቶች ለሰደቃ የመተባበር ጥሪ ጀመዓ!!

Address

Katlehong
1431

Telephone

+27620874630

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Selaam tv group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Selaam tv group:

Share