አማራ ታሪኩን በልጆቹ ይፅፋል _Ethiopia

አማራ ታሪኩን በልጆቹ ይፅፋል _Ethiopia ይህ ፔጅ የተቋቋመበት አላማ በየቦታው በግፍ እየተሰቃየ ላለው የአማራ ህዝብ እንዲሁም ድምፅ ሚሆናቸው ላጡ ኢትዮጵያዊያን ድምፅ ለመሆን ነው።

03/07/2025

መሸነፍ እና መታከት የትግላችን መዝገበ ቃላት ውስጥ የሉም። የአማራን ትላንት በቅጡ ያነበበ እና የተረዳ፤ የአማራን ዛሬ በሚገባ የተነተነ፤ የአማራን ነገ በጥንቃቄ የተለመ መሪ ይዘን የማንወጣው አረንቋ፤ የማንሻገረው ማዕበል የለም።

ይህ ትግል ብዙ አስከፊ ገጠመኞች፣ ብዙ ጀግኖች የሰሩት ተዓምር፣ ብዙ ገራሚ ክስተቶች ድር እና ማግ ሆነው ያቆሙት ቅዱስ ትግል ነው። ትግሉ በስርዓት እንዳይመራ እንቅፋት እየሆኑ ያሉት ከቅርብም ከሩቅም የእግዜር እንግዳ ብለው የተከሰቱ፣ የእናቶች ማቅ መልበስ የማያሳስባቸው፣ አንገታም ወንድሞቻችን በየአውደ ግምባሩ ጠላትን ተናንቀው ሲወድቁ ያላዩ፣ ለህዝብ እንዳልታገልን ሁሉ ለአንዱ ሜዳሊያ ሲታደል ለጥቂቶቻችን ደሞ ሞት ሲፈረድብን እንደነበረ የዘነጉ፣ በአጠቃላይ የትግሉን ምሬት እና ጣዕም የማያውቁ ናቸው።

ዛሬም እንደ አርዓያ የምናያቸው እንደ ወንድም የምናምናቸው ታጋዮች በየቀጠናው አሉ። አንድነቱ እንዳይፀነስ የነበረውን ግድግዳ ለማፍረስ ብዙ ዋጋ ከፍለን የምጥ ግዜው ላይ ደርሰናል። ግብግቡ የጨነገፈ ልጅ ይወለድ ወይስ ጤናማ ልጅ የሚለው ነው።

እጁን መሰብሰብ ያለበት እጁን ያነሳል፤ ከላኪወቹ የተሸከመውን ፕሮጀክት ሳይሆን የፋኖን ፕሮጀክት ሊያሳካ የሚፈልግ ካለ አብሮን ይታገላል። ይህ ትግል እንደ መንፈቅ ህፃን ልዩ ክትትል የሚፈልግ እንጅ የማንም ቅዠታዊ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ አይደለም።
አስረስ ማረ✍️

በዚህ አራት ቀን የአብይን ሰራዊት እንደ ቅጠል አርግፈነዋል። ምሽጎችን ተቆጣጥረናል ፣አዋጊዎችን ማርከናል፣ ከተሞችን ተቆጣጥረናል ።በዚሁ ጎን ለጎን ኮማንዶዎችን አስመርቀናል።
30/06/2025

በዚህ አራት ቀን የአብይን ሰራዊት እንደ ቅጠል አርግፈነዋል።

ምሽጎችን ተቆጣጥረናል ፣አዋጊዎችን ማርከናል፣ ከተሞችን ተቆጣጥረናል ።

በዚሁ ጎን ለጎን ኮማንዶዎችን አስመርቀናል።

ሕዝብ አወያይተን ፣ ምሽግ ተቆጣጥረን ፣ጦር አሰልጠነን አስመርቀን ፣ማርከን ታጥቀናል።
30/06/2025

ሕዝብ አወያይተን ፣ ምሽግ ተቆጣጥረን ፣ጦር አሰልጠነን አስመርቀን ፣ማርከን ታጥቀናል።

ከአማራ ፋኖ በጎጃም ለትራንስፖርት ባለ ንብረቶች እና መንገደኞች የተሰጠ አስቸኳይ ማሳሰቢያ ሰሞኑን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአረመኔው አገዛዝ ወደ ጎጃም መግባቱን ተከትሎ በበርካታ አካባቢዎች አ...
30/06/2025

ከአማራ ፋኖ በጎጃም ለትራንስፖርት ባለ ንብረቶች እና መንገደኞች የተሰጠ አስቸኳይ ማሳሰቢያ

ሰሞኑን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአረመኔው አገዛዝ ወደ ጎጃም መግባቱን ተከትሎ በበርካታ አካባቢዎች አውደ ውጊያዎች እየተካሄዱ ይገኛል ።

በአረመኔው አገዛዝ ላይ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ከማድረስ አልፈን በየ አካባቢው ሰርጎ የገባውን ሐይል በድምሰሳ እና በመማረክ በገባበት የመዋጥ ዘመቻ እያደረግን እንገኛለን ።

በዚህም በአንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያዎች ጎጃም ውስጥ መንገድ እንደተዘጋ ተደርጎ እየተራገበ መሆኑን አረጋግጠናል ።

ነገር ግን ምንም አይነት የተሽከርካሪ እገዳ ያላደረግን መሆኑን እና መንገዶች ለአሽከርካሪዎች እና ለተጓዦች ክፍት መሆናቸውን እንገልፃለን ።

ድል ለጀግናው ህዝባችን
ድል ለጀግናው ፋኖ !!

አዲስ ትውልድ ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣ አዲስ ተስፋ

የአማራ ፋኖ በጎጃም !!

አብይ አህመድ ስልጣን ከያዘ ወዲህ ትላልቅ ኦፕሬሽን አቅደው አሳክተዋል የተባሉ መኮንኖች የተሳተፉበትን የፋኖ አመራር የመምታት ልዩ ኦፕሬሽን ለሶስት ቀናት በአስደናቂ ሁኔታ መከላከል ችለናል።...
29/06/2025

አብይ አህመድ ስልጣን ከያዘ ወዲህ ትላልቅ ኦፕሬሽን አቅደው አሳክተዋል የተባሉ መኮንኖች የተሳተፉበትን የፋኖ አመራር የመምታት ልዩ ኦፕሬሽን ለሶስት ቀናት በአስደናቂ ሁኔታ መከላከል ችለናል።

በዛሬው ዕለት በጠዋቱ በተጀመረ መልሶ ማጥቃት እንደተለመደው የቡድን መሳሪያን ጨምሮ ክላሽ እንደ ጉድ ያፈስንበትን ድል ተቀዳጅተናል።

የአረመኔው ሰራዊት ቁንጮ አብይ አህመድ ስለከሸፈው "የአስገድዶ ማሰለፍ" እቅድ የህዝቡን ጆሮ በመያዝ በጎን ደግሞ በብርሃኑ ጁላ እና በለገሰ ቱሉ በኩል ሰበር ዜና ሊያስነግር የቋመጠበትን ኦፕሬሽን እንደ ጉም አትነነን ሰራዊቱን ገርፈንለታል። ሰከላ ላይ በተሰራ ኦፕሬሽንም በመቶወች የሚቆጥሩ የአረመኔው አገዛዝ የግፍ እስረኞችን ማስለቀቅ ተችሏል።

ጠላት ለሳምንታት ያቀደው ይህ ኦፕሬሽን ከየእዞች የተውጣጣ ኃይልን በልዩ ስምሪት የያዘ ለመረጃ፣ ለሎጅስቲክስ እና ለተተኳሽ በርካታ ሚሊየኖች የተበጀተለት ነበር።

ሊከብ መጥቶ ቆራርጠን የከበብነው የአብይ አህመድ አረመኔ አገዛዝ ጠባቂ አንዲት መነኩሴን ጨምሮ ስድስት ንፁሃንን በመድፍ ድብደባ ከመግደሉ በስተቀር በወገን ላይ ይህ ነው የሚባል ጉዳት ሳያደርስ በመፈርጠጥ ላይ ነው። ዝርዝሩን እመለስበታለሁ።
NB: ፎቶው ዛሬ የተመረቁ የገኛ ክፍለጦር የቦቅላ አባይ ብርጌድ ተመራቂወች ናቸው።

በየቀኑ ከምንከውናቸው ስራወች አንዱ እና ዋናው የሰው ሀይል ማብቃት እና የተሻለ ተዋጊ መፍጠር ነው። ዛሬም እንደ ህዝብ የተጋረጠብንን የህልውና  ትግል ሊቀለብስ  የሚችል የኮማንዶ ሀይል አስ...
29/06/2025

በየቀኑ ከምንከውናቸው ስራወች አንዱ እና ዋናው የሰው ሀይል ማብቃት እና የተሻለ ተዋጊ መፍጠር ነው። ዛሬም እንደ ህዝብ የተጋረጠብንን የህልውና ትግል ሊቀለብስ የሚችል የኮማንዶ ሀይል አስመርቀናል።እነዚህ ኮማንዶወች ለበርካታ ወራት ሲሰለጥኑ የቆዩ በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር የተፈተኑ ዘመኑን የዋጁ እንቁ የአማራ ፋኖወች ናቸው። ሀዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለጦር የቦቅላ አባይ ብርጌድ (አንበሳው ሶስተኛ ዙር ኮማንዶ)💪💪💪

አንችው ታመጭው - አንችው ታሮጭው ነው ነገሩ!!በሰልፍ የሚመጣ ለውጥ እንደሌለ አረጋግጠን መስሎን ሰይፍ ያነሳነው??
29/06/2025

አንችው ታመጭው - አንችው ታሮጭው ነው ነገሩ!!

በሰልፍ የሚመጣ ለውጥ እንደሌለ አረጋግጠን መስሎን ሰይፍ ያነሳነው??

29/06/2025

እንዴት ሰነበታችሁ አማራዊያን ግዳጅ ላይ ስለነበርን ነው የጠፋነው ሰሞኑ

ግዳጃችን በሚገባ በድል ተወጠን ተመልሰናል።

የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ሞስኮ ገቡነገሩ ግልፅ ነው ወሳኝ ሰዓት ላይ ሚንስተሩ ከሩሲያው አለቃ ጋር አንዳች ሊያቅዱት ያለ ነገር እንዳለ ግልፅ ነው።
22/06/2025

የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ሞስኮ ገቡ

ነገሩ ግልፅ ነው ወሳኝ ሰዓት ላይ ሚንስተሩ ከሩሲያው አለቃ ጋር አንዳች ሊያቅዱት ያለ ነገር እንዳለ ግልፅ ነው።

Welcome to Humera town, Amhara, Ethiopia ‼️
22/06/2025

Welcome to Humera town, Amhara, Ethiopia ‼️

የየመን ከፍተኛ የፖለቲካ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ማህዲ አል-ማሻት፡-"በኢራን ላይ በሚደረገው ወረራ ውስጥ ማንኛውንም ተሳትፎ እንጋፈጣለን ፣ እናም ማንኛውም ሰው ለውሳኔያቸው ዋጋ ይከፍላል።"
22/06/2025

የየመን ከፍተኛ የፖለቲካ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ማህዲ አል-ማሻት፡-

"በኢራን ላይ በሚደረገው ወረራ ውስጥ ማንኛውንም ተሳትፎ እንጋፈጣለን ፣ እናም ማንኛውም ሰው ለውሳኔያቸው ዋጋ ይከፍላል።"

22/06/2025

የአቶ መለስ ዜናዊ 6 አስቂኝ ንግግሮች 😂 ስጎረጉር ካገኘሁት!

1, መለስ ውጭ ሀገር ጉብኝት ላይ እያሉ አንድ ነጭ " እናንተ አፍሪካውያንኮ ዝንጀሮ ነው የምትመስሉ።" ይላቸዋል።
አቶ መለስም መለሱለት " እኛ አፍሪካውያን የዝንጀሮዋን ፊት ስንመስል እናንተ ነጮች ደሞ ቂጧን ትመስላላችሁ።"

2, ጋዜጠኛ..." የአዲስ አበባ ስታድየም ለምን በዘመናዊ መልክ አይታደስም?"
መለስ..." ለመሸነፍ ይህ በቂ ነው።"

3, ጋዜጠኛ... " አንድ ዝነኛ የሀገራችን አትሌት ዜግነቴን ልቀይር ነው ይላል። እርስዎ ምን ይላሉ?"
መለስ..."አይደለም ዜግነት ለምን ፆታውን አይቀይርም!"

4.ጋዜጠኛ... "ኃይሌ ገ/ ስላሴ ኢትዮጵያን መምራት እፈልጋለሁ ይላል። እርስዎ ምን ይላሉ።"
መለስ..."እግር ጭንቅላት አይሆንማ።"

5.ቴዲ አፍሮ እስር ቤት እያለ ስለጤንነቱ ጋዜጠኛ ጠየቃቸውና
መለስም እንዲህ ሲሉ መለሱ..." ቴዲ እስር ላይ ሆኖ ቢታመም እንኳ ከአስራ ሰባቱ መርፌ አንዱን ይወጋል። ጨለመብኝ ካለም ላምባዲናውን ያብራ።"

6.ጋዜጠኛ... " ኢትዮጵያ ውስጥ ለማኝ የበዛው ለምንድን ነው?"
መለስ...''ሰጭው ስለበዛ ነዋ።''

አንዴ ደሞ መለስና አባዱላ እየተጫወቱ አባዱላ " እኔኮ አባቴ 12 አህያ ሽጦ ነው ያስተማረኝ።" ይላል...

መለስ..." አባትህ ይገርማሉ።"

አባዱላ..." እንዴት?"

መለስ..." አንድ አህያ ለማስተማር 12 አህያ መሸጣቸው።" 😂
የትኛው ተመቻቹ

Address

Marshallstown

Telephone

+27781380526

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አማራ ታሪኩን በልጆቹ ይፅፋል _Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አማራ ታሪኩን በልጆቹ ይፅፋል _Ethiopia:

Share