12/20/2025
ጥያቄ ተይቄ ነው
ጥያቄው?
ወንዴ እንዴት ነህ ሰላም ነህ?
ሀክ አድራጊዎቹ ገርመውኛል !
ከሁሉ በላይ የገረመኝ የረዳህን እግዚአብሔርን የገለፅክበት መንገድ ደስ ብሎኛል በፈጠሪ ያለህን እምነትህን ወድጄዋለሁ። እሱን ተስፋ ያደረጉ አያፍሩም።
👉 ሌላው ከሁሉ በላይ የገረመኝ አንተ 3ኛውን ክፍል ፖስት አደርጋለሁ ያልክ ለት የሴት አትሌት ኢንተርቪ አየሁ ገረመኝ ወዲያው አንተም ደግሞ 3ኛውን ክፍል ለነገ ስትል የሆነ ነገር ጫረብኝ። ገረመኝም።
👉 በማግስቱ 3ኛውን ክፍል እንደለቀቅክ ደግሞ ወዲያው አራት ፖስቶች አትሌትክስን በተመለከተ በተለያዩ ሰዎች ተለቀቁ። ከፃፍከው ታሪክ ጋር አነፃፅሬ እንማን እንደሆኑ ለማወቅ አልተቸገርኩም።
አንተ 3ኛውን ክፍል እንደለቀቅህ መልቀቃቸው "አቴሽን ማስቀየሻ ጃም" እንደሆነም ገባኝ።
ይህ ገፅ ለሩጫ ስፖርትችን ያደረገው አስተዋፅኦ ቀላል አይደለም እና ሌላው ይቅር ሩጫን እንወዳለን የሚሉ
በየጊዜው ትንታኔ የሚሰጡ በየጉሩፕ የሚለቁ የአትሌትክስ ወዳጆችም ለምን ዝም አሉም የሚለው ጥያቄ ፈጥሮብኛል?
👉አንተ ምን ትላለህ?
መልስ
ስሜትሽን ሳትደብቂ ስለነገርሽኝ አመግናለሁ!!
ሁሉን ከተረዳሽ በቂ ነው።
✍️ ክፍል 3 ሀከሮቹ !!
👉 ሀከሮቹን ማን አደራጃቸው?
👉 እነማን ናቸው?
የመጨረሻረሻው ክፍል!!
እኛ ጥቃቱ እንደተሞከረብን እግዚአብሔ ገለጠልንና አወቅን።
👉 ማን አደራጃቸው?
ካወቅን በኋላ ፈጣሪ ሰው አዘጋጀ
የተዘጋጀው ሰው ዝርዝር አድርጎ ለእኔ ነገረኝ ፤ ሲነግረኝ አደራጆቹ ሁለት ሰዎች እንደሆኑ አንደኛውን ሰው ነግሮኝ አደኛውን ሌላ ጊዜ እነግርሀለሁ ብሎ ሁለተኛውን ሊነግረኝ ፈቃደኛ አይደለም።
ለምን እንደሆነ አላወኩም እኔም አላጨናነኩትም።
👉 ሀከሮቹ እነማን ናቸው?
በአንዱ ምድብ የተለያዩ ፍላጎቶች ያሏቸው የተለያዩ ሰዎች ቢሆኑም ዓላማቸው አንድ ነው። ዓላማቸው ገፁን ማጥፋት ነው።
እዚህ ጉሩፕ ውስጥ እንደ ኢትዮራነርስ አይት ስራ የሚሰሩ መረጃው ያላቸው ለዚህም ስራ እየፈሩ የተሳተፉም አሉበት አውቀናል።
👉 ሁለተኛው ምድብ ላይ ከደላላው እና ሚስጥሩን ከሚያውቁ በስተቀር ሀከሩና አጃቢዎቹ ስለ ስፖርቱ የሚያውቁት ጉዳይ የለም ዱዳ ናቸው። እንጀራ ፍለጋ የመጡ ናቸው በእነሱ አላዝንም።
👉 ነገር ግን ያሰማራቸው ሰው ግን ትልቁን ሀላፊነት ይወስዳል።
ነገሮችን በጊዜው የገለጠልኝ እግዚአብሔር ፤ እኔ ከማንም የሚበልጥ እምነት ኖሮኝ አይደለም ። ነገር ግን እጅግ በጣም በጣም ፈረሀ እግዚአብሔር እንዳላኝ እሱ ቸሩ መድሀኒያለም ውስጤን ፤ልቤን፤ የሚያውቅ ስለሆነ "ላልተገባ ነገር አሳልፍ እንማይሰጠኝ" የሚወረወርብኝ ፍላፃም እንደማያገኘኝ 100% አውቃለሁ።
ውድ የዚህ ገፅ ተከታታዩች መቼስ የሰው ልጅ የክፋት ጥጉ ምን ያህል እንደሆነ ተመልክታችኋል ፤ ነገር ግን
እንዳትፈርዱባቸው!!
ምክንያቱም
የሰው ልጅ እምነቱ ይለያያል፤
የግድ የሰው ሁሉ እምነት የእኔ አይነት እምነት ይሁን አይባልም።
እነዚህ ሰዎች ፦
👉በቤታቸው ሰላም የሚመጣው፤
👉ጤናቸው የሚስተካከለው፤
👉እድገት የሚያገኙት፤
👉ገንዘባቸው የሚባረከው፤
👉ነገሮቻቸው የሚከናወኑት፤
👉የዘሩት ዘር የሚባረከው፤
👉ልጆቻቸው ታንፀው የሚያድጉት፤
👉ልጅ ከሌላቸው በልጅ ትባረካላችሁ የተባሉት፤
እንዲህ አይነት ስራና ሌላም ክፋት ሲሰሩ ሊሆን ስለሚችል አትፍረዱባቸው።
ምክንያቱም መንፈሱ የሚያዛቸውን ነው የሚያደርጉት። ክፉ መስራት የፀሎታቸው አካል ሊሆን ይችላል።
👉 ስለዚህ እንደዚህ አይነት ሰው መሳይ ሰዎችን አንድ ቀን "ሰው" እንዲሆኑ መፀለይ ብቻ ነው።
የሄዱበት መንገድ ጥልቅ ነው ከእነሱ ጥልቅ ስራ ይልቅ ጥልቁን ስራ የገለጠልኝ እግዚአብሔር ስለሚበልጥ ፈጣሪን አመስጋኝ ነኝ።
ባገኘሁት መረጃ መሰረት ገፁን እንዲያጠፉ በደላላው በኩል ያሰማራቸው
ያደራጃቸው ሰው ዋናው።
"የማናጀር ተወካይ ነው።"
"የደላላው የስራ ቦታ ፌ***ን ውስጥ ነው።
ስለ እሱ ጥግብ ያለ መረጃ በእጃችን አለ።
አብረውት የሚሰሩትን የተወሰኑትን ሰዎች በክፍል ሁለት ላይ ስማቸውን መናገር እስኪቀረኝ ድረስ በምልክት ያስረዳሁት ጥቆማ ነው። ሰው ሁሉ እንዲጠነቀቅ ከማሰብም ነው ።
ያወቁትን ማሳወቅ መልካም ስለሆነም ነው።
ስማቸውን የማንገልፅበት ምክንያት ማስረጀ ስለሌለን አይደለም በሚገባ አለን ግን ሌላ ምክንያት ስላለ ነው ሁሉ አይወራም።
አሁን ላይ "ከ ሁ ሉ ም" ጋር ተግባብተናል አየሩ ሰላም ነው!!
እንደ ርቀት ትምርህት ሁሉ ነገር ከማንም ጋር በርቀት ይሆናል።
ኳስ በመሬት !!!
የረዳን እግዚአብሔር ይመስገን!!
ቸር እንሰንብት።