Ethio runners

Ethio runners An official social media Page Athletic news, Biography Writing, Analysis and reporting

Provide updated Athletic news
Athletic Biography Writer
Athletic Sport Analysis/Writer
Athletic Sport Reporter

46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ውድድር እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 10/2026 በአሜሪካን አገር ፍሎሪዳ ከተማ እንደሚካሄድ ይታወቃል ።በመሆኑም የውድድሩ መርሀግብር ከተለመደው ጊዜ ወደ ሶስት ወር ቀደ...
08/10/2025

46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ውድድር እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 10/2026 በአሜሪካን አገር ፍሎሪዳ ከተማ እንደሚካሄድ ይታወቃል ።

በመሆኑም የውድድሩ መርሀግብር ከተለመደው ጊዜ ወደ ሶስት ወር ቀደም ብሎ ስለተያዘ 43ኛው የጃንሜዳ አገር አቋራጭ ውድድር ህዳር 7/2018 ዓ.ም ስለሚካሄድ የማጣሪያ ውድድራችሁን ከጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ውድድር ከሁለት እስከ ሶስት ሳምንት በፊት በማድረግ ተዘጋጅታችሁ በውድድሩ ላይ እንድትሳተፋ በአክብሮት እናሳስባለን ።
መረጃው የኢ አ ፌ ነው።

👉 ከአትሌትነት ወደ እናትነት !እስኪ በአንድ ቃል ግለጿት!!
08/09/2025

👉 ከአትሌትነት ወደ እናትነት !
እስኪ በአንድ ቃል ግለጿት!!

የቶኪዮ የአለም  አትሌትክስ ሻፒዮና ምርጫን እንዴት አየኸው? የቶኪዮ የአለም አትአትሌትክስ ምርጫን በተመለከተ  በ10ሺህ ሜ ምርጫና በማራቶን በተመረጡ አትሌቶች እስማማለሁ ።የምስማማበት ምክ...
08/08/2025

የቶኪዮ የአለም አትሌትክስ ሻፒዮና ምርጫን እንዴት አየኸው?

የቶኪዮ የአለም አትአትሌትክስ ምርጫን በተመለከተ በ10ሺህ ሜ ምርጫና በማራቶን በተመረጡ አትሌቶች እስማማለሁ ።

የምስማማበት ምክንያት በተለይ 10ሺ መስፈረቱና ህጉ በግልፅ ስለተቀመጠ ነው።

በሌሎች ርቀቶች ምርጫ ዙሪያ የተብራራ ነገር በግልፅ አልተቀመጠም አልተነገረም።

በግልፅ አልተቀመጠም አልተነገረም ማለት ግን የመምረጫው ህግ የላቸውም ለማለት አያስደፍረም። ምክንያቱም የተወሰነውን የመምረጫ ህግ ማሳወቅ የተወሰነውን ደግሞ አለማሳወቅ የአሰራሩ አንዱ አካሄድ ሊሆን ይችላልና ነው።

ስህተት ይኖራል የሚል እምነት የለኝም ግን ምን አልባት ስህተት እንኳ ካለ ስራ ስትሰራ ሁል ጊዜ ትክክል ላትሆን ትችላለህ ነገር ግን ስህተትን አምኖ ከስህተት ለመታረም መዘጋጀተና ለስህተቱም ይቅርታ መጠየቅ የአዋቂነት ጥግ ነው እላለሁ ። ምክንያቱም በይቅርታ ውስጥ ምህረት አለና ነው።

በተመረጡት አትሌቶች ዙሪያ አስተያየት ለመስጠት የሆነ መነሻ ሀሳብ ያስፈልጋል ፤ የመነሻ ሀሳቡን ይዘህ እንዲህ ነው ልትል ትችላለህ እንደገናም ከአሁን በኋላም ምን እንደሚፈጠር ምንም በማይታወቅ ነገር ከምናገር ግራ እንደገባኝ እቀመጣለሁ እንጂ እኔ ግራ ተጋብቼ ተከታታዮቼንም ግራ ማጋባት አልፈልግም። ሲጠቀለል ምንም አስተያየት የለኝም።

ግን አይሆንም እንጂ ቢሆን ብዬ ለወደፊት የምመኘው

ከሚቀጥለው አመት በኋላ የሚካሄዱ አለም አቀፍ ውድሮች ላይ የሚሰለፉ አትሌቶችን የሚመርጡበትን ቋሚ መስፈርት ዝርዝር አሁኑኑ በዚሁ ወር በ2025 ቢያሳውቁን ወይም ቢለጥፉልን።

ነገሮች ሁሉ ግልፅ ይሆናሉ የሚል የግል አምነት አለኝ።

ችግር እየተፈጠረ ያለው ከተሮጠ በኋላ ህግ እየወጣ ነው።

አዲስ የመጣው የስራ አስፈፃሚ ለቦታው አዲስ ነው 8 ወሩ ነው ማድረግ የነበረት እስኪረጋጋ ድረስ ለ2025 የአለም አቀፍ የአትሌት ምርጫ በነበረው አሰራር ቀጥሎ ከሚቀጠለው ከ2026 አመት በኋላ ግን የራሴ ይሻላል የሚለውን የአመራረጥ ዘይቤውን አሁን ላይ በ2025 ቢያሳውቅ ኖሮ ግልፅና ግልፅ ይሆንለት ነበረ።

ፌደረሽኑ ወጪ ቁጠባ ላይ እየሰራ ነው በተለይ የውጪ ጉዞ ላይ እየተባለ ይነገራል

ትክክል ነው።

እደግፈዋለሁ ።

ግን ወጪ ቁጠባ ሲባል ሁሉንም ያካትታል እና የስራ አስፈፃሚዎች የሚውዱት የትጥቅ አወሳሰድ ክፍተት ላይ ጠንክሮ እንዲሰራ እናሳስባለን።

መልካም ዕድል ለቶኪዮ 2025 ቡድን!!

Happy Birthday!መልካም ልደት!እንኳንም ተወለድ➙አትሌት አበበ ቢቂላ ይባላል!!➙ ኦለፒያን ነው➙ የኢትዮጵያ የማራቶን አባት!!!!➙ ለእስካሁን ላሉ የዘመናችን አትሌቶች ፈር ቀዳጅ ከመ...
08/07/2025

Happy Birthday!
መልካም ልደት!
እንኳንም ተወለድ
➙አትሌት አበበ ቢቂላ ይባላል!!
➙ ኦለፒያን ነው
➙ የኢትዮጵያ የማራቶን አባት!!!!

➙ ለእስካሁን ላሉ የዘመናችን አትሌቶች ፈር ቀዳጅ ከመሆን ያለፈ ታሪክ ያለው ፤ኢትዮጵያ የመሮጥ አቅም እንዳላት አይደለም ማሸፍ እንደምትችልም ለአለም ህዝብ በታላቁ ኦሊምፒክ የገለጠ የመጀመሪው የኢትዮጵያ ባለ ክብር አትሌት ነው።

➙ ማራቶንን በባዶ እግሩ መሮጡ ደግሞ ሌላ ግርምት የፈጠረ አትሌት ነው።

➙አትሌቱ በኢንተርናሽናል ደረጃ እ ኤ አ ከ1960 እስከ 1968 ለ8 አመት በሩጫ ላይ ቆይቶ 10 ውድድሮችን አድርጓል።

በተደጋጋሚ ብዙ የሮጠቻቸው ርቀት ማራቶን ነው 9 ጊዜ ሮጧል። 10ሺህ ሜትርን 1 ጊዜ በጀርመን በርሊን ISTAF, Berlin እ ኤ አ በ1962 ሮጦ 29:00. 8h PB በመሮጥ
2ኛ ደረጃን አግኝቶ ጨርሷል።

ዘጠኝ ማራቶን የሮጠባቸው ቦታዎችና የገባባቸው ሰዓቶች

➙ሮም ኦሊምፒክ OG, Roma እ ኤ አ 10 Sep 1960 የገባበት ሰዓት 2:15:16 PB ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ግሪክ Athína እ ኤ አ 7 May 1961 የገባበት ሰዓት 2:23:44 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ስሎቫኪያ Košice እ ኤ አ 8 Oct 1961 የገባበት ሰዓት 2:20:12 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙አሜሪካ ቦስተን ማራቶን እ ኤ አ 1963 የገባበት ሰዓት 2:24:43 ያገኘው ደረጃ 5ኛ

➙ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ አዲስ አበባ ላይ ኦገስት 3/1964 የገባበት ሰዓት 2:16.18 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ቶኪዮ ኦሊምፒክ OG, Tokyo እ ኤ አ 21 Oct 1964 የገባበት ሰዓት 2:12.11 PB ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ቶኪዮ ማራቶን እ ኤ አ 9 May 1965 የገባበት ሰዓት 2:22:55 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ሴኡል ማራቶን እ ኤ አ 30 Oct 1966 የገባበት ሰዓት 2:17:04 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ሜክሲኮ ኦሊምፒክ OG, México
እ ኤ አ 20 Oct 1968 DNF (አቋረጠ)

➙ ሀገሩ ኢትዮጵያን 3 ጊዜ በኦሊምፒክ ወክሏል። በ3 ጊዜ ውክልናው 2 ወርቅ ወስዷል።

በኦሊምፒክ ታሪክ ማለትም እ ኤ አ ከ1956 እስከ 2024 በተካሄዱ ኦሊምፒኮች ከኢትዮጵያዊን አትሌቶች ውስጥ ለሀገሩ ብዙ ሜዳሊያዎችን በማግኘት በሁለት ወርቅ 6ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ታሪክ 39 ሜዳሊያዎችን አግኝታለች ለእኔ ሰለሳ ዘጠኙም ሜዳሊያ የአበበ ቢቂላ ነው ብዬ ነው የማምነው።
Photo
Abebe Bikila on the podium of the 1964 Tokyo Olympics, after winning gold in the marathon, and surrounded by Basil Heatley of Great Britain (Silver) and Kokichi Tsuburaya of Japan (Bronze

📌ኢትዮ ራነርስ ለኦሊምፒክ ጀግኖች ትልቅ ክብር አለው!!

🇪🇹1960 Gold Abebe Bikila Men's marathon

10 September 2:15:16.2 Rome

🇪🇹 Tokiyo Gold Abebe Bikila Men's marathon 21 October

ዛሬ የጀግናው የፈርቀዳጁ የማራቶን አባት አትሌት አበበ ቢቂላ ልደት ነው

አትሌቱ በዛሬዋ ቀን እ ኤ አ 7 August 1932 ተወለደ።
እ ኤ አ ✝ 25 October 1973 ከዚህ አለም ድካም አረፈ!!!

Happy Birthday!
መልካም ልደት!
እንኳንም ተወለድክ!!

የአበበ ቢቂላ አድናቂ የሆነችሁ በሙሉ እስኪ እንኳንም ተወለድክ በሉት!!
መልካም ልደት!!
💣🥳💖
💣🥳💖


Happy Birthday!
መልካም ልደት!
እንኳንም ተወለድክ!!

መረጃዎች የተጠናከሩበት ገፆች

wikipedia and world athletics pages
Photo Via Getty Images

Wondmagegn Getachew Yigezu

"ነፍሳቸውን ይማርና ዶክተር ወልደመስቀልኮስትሬ እንዲህ አሉ ይባላል!!" አንዱ እንዲህ ብሎ ጠየቃቸው ?ዶክተር እርስዎ የማሰልጠን እውቀቱ አለዎት ግን ለሌሎች ለማስተማር ፈቃደኛ አይደሉም ፤ማ...
08/07/2025

"ነፍሳቸውን ይማርና ዶክተር ወልደመስቀል
ኮስትሬ እንዲህ አሉ ይባላል!!"
አንዱ እንዲህ ብሎ ጠየቃቸው ?

ዶክተር እርስዎ የማሰልጠን እውቀቱ አለዎት ግን ለሌሎች ለማስተማር ፈቃደኛ አይደሉም ፤ማሳየትም አይፈልጉም ይባላል ለምንድን ነው ብሎ ይጠይቃቸዋል?

"እሳቸውም አይ ልጄ ሁሉም አውቃለሁ ብሎ ነው የሚመጣው ለመሆኑ ማን አላውቅም ብሎ የመጣ አለና እንቢ አልኩ አሉ ይባላል።"

የድሮዎቹ አሰልጣኞች ጎበዝ ፤ቆራጥ፤ አቋም ያላቸው፤ የማይወላውሉ ፤ እንኳን ሙያችውን ክብራቸወን የማያስነኩ ጠንካራ አሰልጣኞች ነበሩ።

የአበበ ቢቂላ አሰልጣኝ ሲውዲናዊው Onni Niskanen ንጉሴ ሮባን የመሰለ ቆራጥና ጀግና አሰልጣኝ አፈራ ፤

ንጉሴ ሮባ ፤ እነ ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬን ከእግር ኳስ አሰልጣኝነት አምጥቶ በአትሌትክሱ ጀግና አሰልጣኝ አድርጎ አፈራ፤ አሁንም ንጉሴ ሮባ በእሱ ይሰለጥኑ የነበሩ እነ ተገኝ በዛብህን ፤ ቶሎሳ ቆቱን ፤ ሻንበል እሸቱ ቱራ የመሳሰሉና ሌሎችንም አፈራ፤ ከዚህ በኋላ ያለ ትውልድ ነጥሮ የሚወጣ የሚተካ አሰልጣኝ ጠፋ። አጣን።

በጣም የሚናድድኝ በዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ የሰለጠኑ አትሌቶች ከእሳቸው ብዙ እውቀት አግኝተዋል።

በእሳቸው የስልጠና ዘመን የሰለጠኑ አትሌቶች ጠንካሮች ስለነበሩ ሽልማታቸውም ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት ብዙ ገንዘብ ስላገኙ ወደ ንግዱ አለም ዝንባሌቸው ሆነ ገንዘብ ሲኖር ደግሞ የሚያስመኘው ሌላ ሌላ ቦታ እንጂ እታች ወርዶ አትሌት ማሰልጠን አያስመኝም እና በዚህም ምክንያ ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ ጋር የነበረ የማሰልጠን ጥበብ ቅብብሎሹ አልቀጠለም ተገታ።

በዚህ ምክንያት የማይሰማ የአሰልጣኝ አይነት የለም እድሜ ለቴክኖሎጂ እያንዳንዱ ማኔጅመንት የራሱ የሆነ ሲስተም አለው ሲስተሙ ደግሞ ከ5 አመት በላይ የማይዘልቅ አትሌት እያሳዩን አሉ።

በዶክተር ወልደመስቀል ከሰለጠኑ አትሌቶች ሩጫ ካቆሙ በኋላ ማናጀር ወይም የማናጀር አሰልጣኝ ቢሆኑ ብዙ የትራክ አትሌት ይፈጥሩ ነበረ ብዬ ድሮ ገና የምመኛቸው የነበሩ፦

ሀይሌ ገ/ስላሴ የቀድሞ የፌደረሽን ፕ
ረ/ኮ ደራርቱ ቱሉ የቀድሞ የፌደረሽን ፕ
ኮማንደር ስለሺ ስህን የአሁን የፌደረሽን ፕ
መሰረት ደፋር የአሁን ም/ ፕረ
ብርሀኔ አደሬ የኦሊፒክ ኮሚቴ ም/ፕ
ኮማንደር ጌጤ ዋሚ የአንጋፋ አትሌቶች ፕረዚዳንት ነበሩ ግን ምኞቴ አልሆነም።

📌 ሩጫ ሲያቆሙ አሁንም ተስፋ የጣልኩባቸው ደግሞ
በቀነኒሳ በቀለ እና በጥሩነሽ ዲባባ ተስፋ አልቆርጥም።

Wondmagegn Getachew Yigezu

➙አትሌት አበበ ቢቂላ ይባላል!!➙ ኦለፒያን ነው➙ የኢትዮጵያ የማራቶን አባት!!!!➙ ለእስካሁን ላሉ የዘመናችን አትሌቶች ፈር ቀዳጅ ከመሆን ያለፈ ታሪክ ያለው ፤ኢትዮጵያ የመሮጥ አቅም እንዳ...
08/07/2025

➙አትሌት አበበ ቢቂላ ይባላል!!
➙ ኦለፒያን ነው
➙ የኢትዮጵያ የማራቶን አባት!!!!

➙ ለእስካሁን ላሉ የዘመናችን አትሌቶች ፈር ቀዳጅ ከመሆን ያለፈ ታሪክ ያለው ፤ኢትዮጵያ የመሮጥ አቅም እንዳላት አይደለም ማሸፍ እንደምትችልም ለአለም ህዝብ በታላቁ ኦሊምፒክ የገለጠ የመጀመሪው የኢትዮጵያ ባለ ክብር አትሌት ነው።

➙ ማራቶንን በባዶ እግሩ መሮጡ ደግሞ ሌላ ግርምት የፈጠረ አትሌት ነው።

➙አትሌቱ በኢንተርናሽናል ደረጃ እ ኤ አ ከ1960 እስከ 1968 ለ8 አመት በሩጫ ላይ ቆይቶ 10 ውድድሮችን አድርጓል።

በተደጋጋሚ ብዙ የሮጠቻቸው ርቀት ማራቶን ነው 9 ጊዜ ሮጧል። 10ሺህ ሜትርን 1 ጊዜ በጀርመን በርሊን ISTAF, Berlin እ ኤ አ በ1962 ሮጦ 29:00. 8h PB በመሮጥ
2ኛ ደረጃን አግኝቶ ጨርሷል።

ዘጠኝ ማራቶን የሮጠባቸው ቦታዎችና የገባባቸው ሰዓቶች

➙ሮም ኦሊምፒክ OG, Roma እ ኤ አ 10 Sep 1960 የገባበት ሰዓት 2:15:16 PB ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ግሪክ Athína እ ኤ አ 7 May 1961 የገባበት ሰዓት 2:23:44 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ስሎቫኪያ Košice እ ኤ አ 8 Oct 1961 የገባበት ሰዓት 2:20:12 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙አሜሪካ ቦስተን ማራቶን እ ኤ አ 1963 የገባበት ሰዓት 2:24:43 ያገኘው ደረጃ 5ኛ

➙ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ አዲስ አበባ ላይ ኦገስት 3/1964 የገባበት ሰዓት 2:16.18 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ቶኪዮ ኦሊምፒክ OG, Tokyo እ ኤ አ 21 Oct 1964 የገባበት ሰዓት 2:12.11 PB ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ቶኪዮ ማራቶን እ ኤ አ 9 May 1965 የገባበት ሰዓት 2:22:55 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ ሴኡል ማራቶን እ ኤ አ 30 Oct 1966 የገባበት ሰዓት 2:17:04 ያገኘው ደረጃ 1ኛ

➙ሜክሲኮ ኦሊምፒክ OG, México
እ ኤ አ 20 Oct 1968 DNF (አቋረጠ)

➙ ሀገሩ ኢትዮጵያን 3 ጊዜ በኦሊምፒክ ወክሏል። በ3 ጊዜ ውክልናው 2 ወርቅ ወስዷል።

በኦሊምፒክ ታሪክ ማለትም እ ኤ አ ከ1956 እስከ 2024 በተካሄዱ ኦሊምፒኮች ከኢትዮጵያዊን አትሌቶች ውስጥ ለሀገሩ ብዙ ሜዳሊያዎችን በማግኘት በሁለት ወርቅ 6ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ታሪክ 39 ሜዳሊያዎችን አግኝታለች ለእኔ ሰለሳ ዘጠኙም ሜዳሊያ የአበበ ቢቂላ ነው ብዬ ነው የማምነው።

📌ኢትዮ ራነርስ ለኦሊምፒክ ጀግኖች ትልቅ ክብር አለው!!

🇪🇹1960 Gold Abebe Bikila Men's marathon

10 September 2:15:16.2 Rome

🇪🇹 Tokiyo Gold Abebe Bikila Men's marathon 21 October

ዛሬ የጀግናው የፈርቀዳጁ የማራቶን አባት አትሌት አበበ ቢቂላ ልደት ነው

አትሌቱ በዛሬዋ ቀን እ ኤ አ 7 August 1932 ተወለደ።
እ ኤ አ ✝ 25 October 1973 ከዚህ አለም ድካም አረፈ!!!

Happy Birthday!
መልካም ልደት!
እንኳንም ተወለድክ!!

የአበበ ቢቂላ አድናቂ የሆነችሁ በሙሉ እስኪ እንኳንም ተወለድክ በሉት!!
መልካም ልደት!!
💣🥳💖
💣🥳💖


መረጃዎች የተጠናከሩበት ገፆች

wikipedia and world athletics pages
Photo Via world athletics

✍️ Wondmagegn Getachew Yigezu

➙ የምናየውና የምንሰማው  አልገናኝ እያለን ተቸገርን ምን ይሻላል?     ፌደረሽኑ በግንቦት ወር 2017 ለ10 ሺ ሜ ዕጩዎች ያወጣው መስፈርትና ህግ በገፅ ላይ ለጥፎ ነበረ የለጠፈውን ተመል...
08/05/2025

➙ የምናየውና የምንሰማው አልገናኝ እያለን ተቸገርን ምን ይሻላል?
ፌደረሽኑ በግንቦት ወር 2017 ለ10 ሺ ሜ ዕጩዎች ያወጣው መስፈርትና ህግ በገፅ ላይ ለጥፎ ነበረ የለጠፈውን ተመልከቱና ፍርድ ስጡ!
የተለጠፈውን ሙሉውን ያንብቡ
የዓለም አትሌቲክስ ባስቀመጠው የሚኒማ ማምጫ ጊዜ ማለትም ከፌብሩዋሪ 25/2024 ጀምሮ የተመዘገቡ ሚኒማዎች ለመምረጫ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ይሆናሉ ይላል።
ስለዚህ በ2024 ጁን 14 የተሮጠው 10ሺ ሜትር ሰአት የተሻለ ስለሆነ የተሻለ ስለሚል ተቀባይንተን አግኝቶ የሚከተሉትን አትሌቶች መረጥን ነው የሚሉት
ዮሚፍ 26:31.01
በሪሁ 26:31.13
ሰለሞን 26:34.93 ነው
ስለዚህ የ10 ሺ ሜ ጉዳይ በቃለ ጉባኤው ላይ የተሻለ ሰዓት በሚለው መሰረት ቢንያም በ2025 ቢያሸንፋቸውም የገባበት ሰዓት 26:43.82 በመሆኑ ሰዓቱ ፈጣን ስላልሆነ በተሻለ በሚለው አልተመረጠም ማለት ነው። ያስኬዳል እስማማለሁ።
ነገር ግን በጣም የሚገርመው አዲሱ የስራ አስፈፃሚ 10ሺ ሜትርን የመመረጫ ህጉን ካለው ችግር አኳያ አሻሽሎታል አሳውቀውናል ትክክል ነው ።ያሳማማኛል ። 10ሺ ሜትርን ለይተው ሲያሳውቁ ሌሎች ርቀቶች በድሮው መርጠዋል ማለት ነው አንድምታው።
ቀሪ ርቀቶች ላይ እንደ 10ሺው ደንብ አውጥተው ተናግረዋል ተሳስቼ ከሆነ እንናተ ሰምታችኋል ? በምን መረጡ?
በድሮው መስፈርት ነው የመረጡት ማለት ነው እንዳልል አይገናኝም?
የገባችሁ አስረዱኝ።
ለእኔ የ10ሺህ ሜትር ምርጫ አላወዛገበኝም
ምክንያቱም የተፃፈ ነገር በማስረጃ ስላየሁ።
ያልገባኝ የሌላው ርቀት ምርጫ ነው።

ሰላም ሁኑ!!

ምን ያህል ብር በአካውንታቸው ተሰበሰበላቸው?512,822.71 ብር በአካውንታቸው ገብቷል!!     በመጀመሪ ጥሪዬን አክብራች ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ ሁላችሁንም በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ...
08/04/2025

ምን ያህል ብር በአካውንታቸው ተሰበሰበላቸው?
512,822.71 ብር በአካውንታቸው ገብቷል!!
በመጀመሪ ጥሪዬን አክብራች ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ ሁላችሁንም በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ !! ዘመናችሁ ይባረክ ብያለሁ!!!
የአባዲ ቤተሰብም ቃላት እያጠራቸው አመስግነዋል!!
ቃል የገቡ ስላሉ በየማኔጅመንቱም ሊረዱ ያሰቡ ስላሉ ድጋፉ ይቀጠላል!!

ምክንያቱም የተሰበሰበው ገንዘብ ነገ የሚያልቅ ነውና እግዚአብሔር ቢፈቅድና ሀሳባችን ቢሳካ በተሰበሰበላቸው ገንዘብ በሚኖሩበት አካባቢ ቋሚ ነገር ተገዝቶ ወርሀዊ የማያቋራጥ ገቢ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው ። ይህ እንዲሳካ በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በፀሎትም ታግዙናላችሁ የሚል እምነት አለን።

ምን አልባት ምን ይታወቃል አባዲኮ በህይወት ቢኖር በቶኪዮ የሚሳተፈው ቡድን አባል ይሆን ነበረ

በማለት ለቶኪዮ የተመረጡ አትሌቶች አንድ ላይ በሆቴል ስላሉ ከሚያገኟት አበል ላይ አሰባስበው ሊረዱም ይችላሉ?

አንዳንድ ማናጀሮች ለምን ይዋጣላቸዋል?

አባዲ ማናጀሮቹ ጋር ገንዘብ አለው አይደም ወይ ? ገንዘቡን ማስመለስ አይሻልም ወይ? ያሉኝ አሉ

መልሱ

ገንዘቡ እስኪመለስላቸው ድረስ በራብ መሞት የለባቸውም ከሚል ነው እንጂ ሰዎች ተረባርበው ባይረዷቸው ኖሮ የጠየቁን ማናጀሮችን ገንዘብ አበድሩንና ከማናጀሮቹ ሲመለስላቸው እንስጣችኋለን የሚል ሀሳብ እናቀርብ ነበረ!!

ለማንኛውም አሁን የተሰበሰበው ገንዘብ እግዚአብሔር ይመስገን ከመራብ አላቋቸዋል።

አሁንም ከሁሉም ማኔጅመንት ቡድን አባላት ለአባዲ ቤተሰብ መዋጮ እጠብቃለሁ!!

በተለይ ከህሉፍ ይደጎ ቡድን ብዙ እጠብቃለሁ ምክንያቱም ህሉፍ እንደነገረኝ ከሆነ ህሉፍ ጋር ችግር የለም። ፔኔዳ ነው መልስ መስጠት ያለበት።

ስለዚህ ህሉፉ የሚሳራቸውን አትሌቶች አንዲሁም የቶኪዮ ቡድኑን ህሉፍ አስተባብሮ ታሪክ ይሰራል የሚል እምነት አለኝ።

ደግሞም ህሉፍና አባዲ ጋደኛሞች ናቸው አባዲ ለህሉፍ ባለውለታው ነው ለህሉፍ እዚህ መድረስ ትልቁን አስተዋፅኦ ያደረገው አባዲ ነው ከግሎባል ወቶ ወደ ህሉፍ ሲመጣ ብዙ አትሌቶች ወደ ህሉፍ እንዲመጡ ምክንያት ሆኗል በዚህም ምክንያት ህሉፍ የአባዲ ቤተሰቦች ሲቸገሩ አይቶ ይጨክናል የሚል እምነት የለኝም።

ምን ይታወቃል ?
ወንዴ በቃህ ልምና ብሎ
እኛ ለቤተሰቦቹ ያሰብነውን ቋሚ ገቢ ህሉፍ ሊሸፍነው ይችላል!!

👉 ህሉፍ በቶኪዮ ለሚካሄደው የዓለም ሻፒዮና ቡድን ቡዙ አትሌቶችን በማስመረጥ ግንባር ቀደሙ ነው።

👉 ማናጀሮቹ ጋር ስላለው ገንዘብ የማስመለስ ሂደት ለሁለተኛ ጊዜ ፌደረሽኑ ማናጀሮቹን ጠይቋቸው መልስ ሊሰጡት አልቻሉም። መልስ ያለመስጠታቸው ለምን እንደሆነ ከፌደረሽኑ ውጪ የሚያውቅ የለም።

ምክንያቱም አትሌቱ የፌደረሽኑ ልጅ ነው፤ ለማናጀሩ ከልጁ ጋር አብሮ እንዲሰራ ፈቃድ የሰጠው አካል ፈደረሽኑ ነው።

ስለዚህ የመጠየቅ መብት ያለው ፌደረሽኑ ነውና እኛ በሰከነ መንፈስ ሆነን ፌደረሽኑን የሚወስደውን እርምጃ መጠበቅ ምርጫ የሌለው ምርጫችን ነው።

አባዲ በትውልድ ቀየው የገዛው መሬት

ችግሩ አልተፈታም ገዢዎቹ ፍርድ እንዲዛባ እንዲዘገይ በተለያየ መንገድ እየሄዱ ነው ይህን ለሚያስፈፅምላቸው ደላላም ሆነ ዳኛ ከ1ሺ ካሬው ላይ 300 ካሬ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። ይህን ጉዳይ የአትሌቶች ማህበር ዝም ሊል አይገባም ።

📌 በዚህ አጋጣሚ መናገር የምፈልገው የአለም ሻፒዮናው እስኪጠናቀቅ ድረስ አትሌቶች እንዳይረበሹ ከማሰብ የአባዲን ጉዳይ አናነሳም።
ሻፒዮናው ሲያልቅ ግን ይቀጥለል።
እስካሁን የተሰበሰበው ብር
512,822.71 ብር በአካውንታቸው ገብቷል!!
በድጋሜ ሁላችሁንም በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ !!
ዘመናችሁ ይባረክ!!!

✍️ Wondmagegn Getachew Yigezu


ምን ያህል ብር በአካውንታቸው ተሰበሰበላቸው?  ለሚለው ጥያቄ ዛሬ ይገለፃል!! በመጀመሪ ጥሪዬን አክብራች ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ ሁላችሁንም በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ !! ዘመናችሁ ይባ...
08/04/2025

ምን ያህል ብር በአካውንታቸው ተሰበሰበላቸው?
ለሚለው ጥያቄ ዛሬ ይገለፃል!!
በመጀመሪ ጥሪዬን አክብራች ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ ሁላችሁንም በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ !! ዘመናችሁ ይባረክ ብያለሁ!!!
የአባዲ ቤተሰብም ቃላት እያጠራቸው አመስግነዋል!!
ቃል የገቡ ስላሉ በየማኔጅመንቱም ሊረዱ ያሰቡ ስላሉ ድጋፉ ይቀጠላል!!
ምክንያቱም የተሰበሰበው ገንዘብ ነገ የሚያልቅ ነውና እግዚአብሔር ቢፈቅድና ሀሳባችን ቢሳካ በተሰበሰበላቸው ገንዘብ በሚኖሩበት አካባቢ ቋሚ ነገር ተገዝቶ ወርሀዊ የማያቋራጥ ገቢ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው ። ይህ እንዲሳካ በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በፀሎትም ታግዙናላችሁ የሚል እምነት አለን።
ምን አልባት ምን ይታወቃል አባዲኮ በህይወት ቢኖር በቶኪዮ የሚሳተፈው ቡድን አባል ይሆን ነበረ
በማለት ለቶኪዮ የተመረጡ አትሌቶች አንድ ላይ በሆቴል ስላሉ ከሚያገኟት አበል ላይ አሰባስበው ሊረዱም ይችላሉ?

አንዳንድ ማናጀሮች ለምን ይዋጣላቸዋል?
አባዲ ማናጀሮቹ ጋር ገንዘብ አለው አይደም ወይ ? ገንዘቡን ማስመለስ አይሻልም ወይ? ያሉኝ አሉ

መልሱ
ገንዘቡ እስኪመለስላቸው ድረስ በራብ መሞት የለባቸውም ከሚል ነው እንጂ ሰዎች ተረባርበው ባይረዷቸው ኖሮ የጠየቁን ማናጀሮችን ገንዘብ አበድሩንና ከማናጀሮቹ ሲመለስላቸው እንስጣችኋለን የሚል ሀሳብ እናቀርብ ነበረ!!
ለማንኛውም አሁን የተሰበሰበው ገንዘብ እግዚአብሔር ይመስገን ከመራብ አላቋቸዋል።

አሁንም ከሁሉም ማኔጅመንት ቡድን አባላት ለአባዲ ቤተሰብ መዋጮ እጠብቃለሁ!!
በተለይ ከህሉፍ ይደጎ ቡድን ብዙ እጠብቃለሁ ምክንያቱም ህሉፍ እንደነገረኝ ከሆነ ህሉፍ ጋር ችግር የለም። ፔኔዳ ነው መልስ መስጠት ያለበት።
ስለዚህ ህሉፉ የሚሳራቸውን አትሌቶች አንዲሁም የቶኪዮ ቡድኑን ህሉፍ አስተባብሮ ታሪክ ይሰራል የሚል እምነት አለኝ።

ደግሞም ህሉፍና አባዲ ጋደኛሞች ናቸው አባዲ ለህሉፍ ባለውለታው ነው ለህሉፍ እዚህ መድረስ ትልቁን አስተዋፅኦ ያደረገው አባዲ ነው ከግሎባል ወቶ ወደ ህሉፍ ሲመጣ ብዙ አትሌቶች ወደ ህሉፍ እንዲመጡ ምክንያት ሆኗል በዚህም ምክንያት ህሉፍ የአባዲ ቤተሰቦች ሲቸገሩ አይቶ ይጨክናል የሚል እምነት የለኝም።
ምን ይታወቃል ?
ወንዴ በቃህ ልምና ብሎ
እኛ ለቤተሰቦቹ ያሰብነውን ቋሚ ገቢ ህሉፍ ሊሸፍነው ይችላል!!
👉 ህሉፍ በቶኪዮ ለሚካሄደው የዓለም ሻፒዮና ቡድን ቡዙ አትሌቶችን በማስመረጥ ግንባር ቀደሙ ነው።

👉 ማናጀሮቹ ጋር ስላለው ገንዘብ የማስመለስ ሂደት ለሁለተኛ ጊዜ ፌደረሽኑ ማናጀሮቹን ጠይቋቸው መልስ ሊሰጡት አልቻሉም። መልስ ያለመስጠታቸው ለምን እንደሆነ ከፌደረሽኑ ውጪ የሚያውቅ የለም።
ምክንያቱም አትሌቱ የፌደረሽኑ ልጅ ነው፤ ለማናጀሩ ከልጁ ጋር አብሮ እንዲሰራ ፈቃድ የሰጠው አካል ፈደረሽኑ ነው።
ስለዚህ የመጠየቅ መብት ያለው ፌደረሽኑ ነውና እኛ በሰከነ መንፈስ ሆነን ፌደረሽኑን የሚወስደውን እርምጃ መጠበቅ ምርጫ የሌለው ምርጫችን ነው።

አባዲ በትውልድ ቀየው የገዛው መሬት
ችግሩ አልተፈታም ገዢዎቹ ፍርድ እንዲዛባ እንዲዘገይ በተለያየ መንገድ እየሄዱ ነው ይህን ለሚያስፈፅምላቸው ደላላም ሆነ ዳኛ ከ1ሺ ካሬው ላይ 300 ካሬ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። ይህን ጉዳይ የአትሌቶች ማህበር ዝም ሊል አይገባም ።

📌 በዚህ አጋጣሚ መናገር የምፈልገው የአለም ሻፒዮናው እስኪጠናቀቅ ድረስ አትሌቶች እንዳይረበሹ ከማሰብ የአባዲን ጉዳይ አናነሳም።
ሻፒዮናው ሲያልቅ ግን ይቀጥለል።

እስካሁን የተሰበሰበው ብር
512,822.71 ብር በአካውንታቸው ገብቷል!!
5መቶ 12ሺህ ስምንት መቶ ሀያ ሁለት ብር ከሰባ አንድ ሰንቲም ገቢ ሆኗል።
በድጋሜ ሁላችሁንም በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ !!
ዘመናችሁ ይባረክ!!
✍️ Wondmagegn Getachew Yigezu

5ኛው ዙር የኬሮድ የ15 ኪሎሜትር ውድድር "ለኢትዮጵያ ሰላም እሮጣለሁ!" በሚል መሪ ቃል በወልቂጤ ከተማ በድምቀት ተካሄደ።የውድድሩ አሸናፌዎች1ኛ. ሀጎስ እዮጋረድ ከዘቢዳር አትሌቲክስ የ12...
08/03/2025

5ኛው ዙር የኬሮድ የ15 ኪሎሜትር ውድድር "ለኢትዮጵያ ሰላም እሮጣለሁ!" በሚል መሪ ቃል በወልቂጤ ከተማ በድምቀት ተካሄደ።
የውድድሩ አሸናፌዎች

1ኛ. ሀጎስ እዮጋረድ ከዘቢዳር አትሌቲክስ የ125 ሺህ ብር
2 ኛ ጋዲሳ ዘውዴ ከኦሮሚያ ፖሊስ የ50 ሺህ ብር
3ኛ ሉሉ በቢ የግል ተወዳዳሪ የ25 ሺህ ብር የተሸለሙ ሲሆን

በሴቶች ደግሞ
1ኛ ጉተሚ ሻንቆ ከኦሮሚያ ፖሊስ የ125 ሺህ ብር
2ኛ ዝማም በረኪ በግል የ50 ሺህ ብር
3ኛ ሌሊሲ በቀለ ከኦሮሚያ ፖሊስ የ25 ሺህ ብር ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን

በህብረተሰብ
1ኛ ወ/ደንበት ረጋ ከወልቂጤ የወርቅ
2ኛ ፀጋዬ ፈርሻ ከእምድብር የብር
3ኛ ታረቀኝ አሜ ከጌታ የነሀስ ሜዳሊያ ተሸልመዋል።

👉 መረጃው የጉራጌ ዞን መንግስት ኮ/ጉ/መምሪያ ነው።

Address

111 N Patsburg Street
Denver, CO
80018

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio runners posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio runners:

Share